August 2, 2015
1 min read

በአማራና በትግራይ ክልል መካከል ያለው መሬትን መነሻ ያደረገ ግጭት የሰውን ሕይወት እየቀጠፈ ነው ተባለ

(ሁመራ ከተማ)
በአማራና በትግራይ ክልል መካከል ያለው መሬትን መነሻ ያደረገ ግጭት የሰውን ሕይወት እየቀጠፈ ነው ተባለ 1

የደህሚት ድምጽ እንደዘገበው በአማራና በትግራይ ክልል መካከል ያለው መሬትን መነሻ ያደረገ ግጭት እስካሁን መፍትሄ ባለማግኘቱ የሰው ህይወት እየጠፋ መሆኑን ተገለፀ።

የአማራና የትግራይ ክልል ነዋሪዎች ከዚህ በፊት በቆየ የመሬት አለመግባባት በተነሳ ግጭት ምክንያት ብዙ ወገኖቻችን እየሞቱ የሁለቱ ክልል የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው ጉዳዩን በትኩረት አይተው እልባት ከመስጠት ይልቅ በቸልተኝነት እያዩት መሆናቸውን የገለፀው መረጃው በዚህ ምክንያትም በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ቃፍታ ሁመራ ወረዳ ግጨው በተባለ ቦታ ሃምሌ 13 ቀን 2007 ዓ/ም ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች አንድ ዜጋ ተገድሎ መገኘቱን ለማወቅ ተችሏል።

ይህ ተገድሎ የተገኘው ወገን የትግራይ ክልል ተወላጅ ሲሆን ሁኔታውን ተከታትሎ የሚያጣራ አካል እንደሌለ የገለፀው መረጃው ይህም ገዢው የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ባለስልጣናት ሁለትም ብሄሮች በግጭት እንዲኖሩና አንድነት እንዳይፈጥሩ ለማድረግና የስልጣን እድሜያቸውን ለማራዘም የሚጠቀሙበት መላ መሆኑን ታውቋል።

1 Comment

Comments are closed.

Previous Story

ኢህአዴግን ለመጣል መጀመሪያ እኛ መውደቅ አለብን

tplf rotten apple 245x300 1
Next Story

«ከመጥረቢያ ብረት የተሰራ ጦር ወደ አቡጀዲ ቢወረውሩት ወደ ጉቶ ይሄዳል»

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop