ኮንዶሚኒየም ፎቅ ላይ የወጣውን ጅብ ለማስወጣት በተከፈተ ተኩስ አንድ ወጣት ቆሰለ

June 12, 2013

በመስከረም አያሌው

በሐያት ኮንዶሚኒየም ሶስተኛ ፎቅ ላይ ወጥቶ አልወርድም ያለውን ጅብ ለማስወጣት በተተኮሰ ጥይት አንድ ወጣት ቆስሎ ሆስፒታል ገባ።
በህንጻው ላይ የሚኖሩ የአይን እማኞች እንደገለፁት፤ ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ አራት ሰዓት ገደማ ወደ ህንጻው በማምራት ሶስተኛ ፎቅ አንድ መኖሪያ ቤት በር ላይ የተኛውን ጅብ ትላንት ለማስወጣት አምስት ጥይቶች ተተኩሰው ጅቡ የተገደለ ሲሆን፤ በአካባቢው የነበረ አንድ ወጣት በነጠረ ጥይት ሆዱ ላይ ተመትቶ ሆስፒታል ገብቷል። ፎቁ ላይ የወጣው ጅብ እስከ ትናንት ከረፋዱ አራት ሰዓት ገደማ ድረስ እዚያው ፎቁ ላይ መቆየቱን የተናገሩት ነዋሪዎቹ ጅቡን እንዳዩት በማስፈራራት ለማስወጣት ቢሞክሩም አልቻሉም። ነዋሪዎቹ ለፖሊስ ስልክ ደውለው ያሳወቁ ሲሆን፤ ፖሊስም “ለአካባቢ ጥበቃ በስልክ ጉዳዩን አሳውቀናል” በማለቱ ጅቡ እዚያው ሊያድር ችሏል።
ጅቡ በህንጻው ላይ እስካለበት ጊዜ ድረስ ፎቁ ላይ የነበሩ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሳይወጡ መቆየታቸውን የገለፁ ሲሆን፤ ትናንት ጠዋት ላይም አንዳንድ ወላጆች በዱላ እና በአንዳንድ ነገሮች ጅቡን እየተከላከሉ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላካቸውን ገልፀዋል። ጅቡ በህንፃው ላይ ሌሊቱን ሙሉ በማሳለፉ ከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ ሆነው ማደራቸውን የገለፁት የህንጻው ነዋሪዎች፤ ጅቡ ከቦታው እስከተነሳበት ሰዓት ድረስም እንደልባቸው በህንጻው ላይ ለመንቀሳቀስ መቸገራቸውን ገልጸዋል። በህንጻው ላይ እንዲህ አይነቱ ነገር ሲፈጠር ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን የገለፁት ነዋሪዎቹ፣ በሁኔታው በጣም መደናገጣቸውን ገልጸዋል።
ጅቡ በህንጻው ላይ ሌሊቱን ሙሉ ካሳለፈ በኋላ እስከ ትናንት ረፋድ አራት ሰዓት ድረስ እዚያው የቆየ ሲሆን፤ አራት ሰዓት ተኩል አካባቢ በፖሊስ አማካይነት በአምስት ጥይቶች ተገድሎ ከህንጻው ላይ ሊወርድ ችሏል።n

(ምንጭ፡-ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 405 ሰኔ 5/2005)

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop