June 6, 2013
3 mins read

የአንድነት የወረዳ 19 ምክትል ሰብሳቢ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል

UDJ Images
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የወረዳ 19 ምክትል ሰብሳቢ ወጣት ባህሩ ራህመቶ ግንቦት 20/2005 ማለዳ ከመኖሪያ ቤቱ በደህንነት አባላት ከተወሰደ በኋላ የሚገኝበት ፖሊስ ጣብያ ሳይታወቅ ለቀናት መቆየቱንና በማረፊያ ቤቱ እንዲቆይ ያደረገው ፖሊስም እስከ ግንቦት 27/2005 ፍርድ ቤት ሳያቀርበው መቆየቱን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡
ሜክሲኮ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በ27/2005 እንዲቀርብ የተደረገው ባህሩ ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 17/2005 ሊያደርገው የነበረን ሰላማዊ ሰልፍ ስትቀሰቅስ ነበር የሚል ክስ እንደቀረበበት ለመረዳት ተችሏል፡፡የፍርድ ሂደቱን የባህሩ ወዳጆች፣ጋዜጠኞችና ታዛቢዎች በሚገኙበት ግልጽ ችሎት እንዲከናወን አለመደረጉም ብዙዎችን አስገርሟል፡፡ባህሩ ፍርድ ቤት በቀረበበት ዕለት የባለ ራዕይ ወጣቶች ማህበር ተቀዳሚ ፕሬዘዳንትና የህዝብ ግኑኝነት ሃላፊ የሆነው ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ለህዝብ ዝግ በሆነ ችሎት ጉዳዩን እንዲከታተል ተደርጓል፡፡
ፖሊስ የእነ ብርሃኑን ክስ ለመምራት የሚያስችለው ስልጣን እንደሌለው በመጥቀስ ሁለት ቀጠሮ የጠየቀበትን ጉዳይ ፍርድ ቤቱ እንዲዘጋለት ቢጠይቅም
ዳኛው የአዲስ አበባ ፖሊስ ክሱን ለፌደራል ፖሊስ እንዲያዞር በማዘዝ ክሱ ለፌደራል ፖሊስ ካልዞረ ግን በ29/5/2005 መዝገቡን በመዝጋት ተጠርጣሪዎቹን በነጻ እንደሚያሰናብቱ አስረድተዋል፡፡የእነ ብርሃኑ ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ‹‹ፍርድ ቤቱ ከፖሊስ የቀረበለትን ጥያቄ በመቀበል ያለ በቂ መረጃ እየተንገላቱ የሚገኙትን ደምበኞቻቸውን በነጻ ማሰናበት ሲገባው ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ እንዳስገረማቸው ገልጸዋል፡፡
የባህሩና የብርሃኑ ቤተሰቦችና የቅርብ ሰዎች ነገ በሚካሄደው የፍርድ ችሎት ሁለቱ ወጣቶች በነጻ ሊሰናበቱ እንደሚችሉ ተስፋ ማድረጋቸውን ለፍኖተ ነጻነት ተናግረዋል፡፡
source:- http://www.fnotenetsanet.com/?p=4543
Likun astatke jpg
Previous Story

ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ ተከሰሱ

UDJ Candlelight vigil
Next Story

ኑ! በገዢው ቡድን በግፍ የተጨፈጨፉ ሰማዕታትን በመዘከር የትግል ቃልኪዳናችንን እናድስ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop