ጥያቄዉ የሃይማኖት ሳይሆን የሰብዓዊ መብት ጥያቄ ነዉ ! አማኑኤል ዘሰላም

አማኑኤል ዘሰላም
amanuelzeselam@gmail.com
የካቲት 8  2013
 

ምንጩ ሳዉዲ አረቢያ የሆነው፣ ከነዳጅ በሚገኝ ሚሊዮን ዶላሮች የሚደገፈውና መረቡን በአለም ዙሪያ ሁሉ የዘረጋዉ፣  የዋሃቢዝም የእስልምና አክራሪነት፣ በአለማችን ትልቅ ችግር እየፈጠረ በብዙ አገሮች አለመረጋጋትን ያመጣ እንደሆነ፣ የአለምን ሁኔታ በቅርበት የሚከታታል ያጣዋል ብዬ አላስብም። አል ሻባብ፣ አል ካይዳ፣ አንሳር አሊዝላም ፣ ቦካ ሃራም  የመሳሰሉ ጸረ-ሰላምና ሽብርተኛ ቡድኖች መሰረታቸው፣ ይሄዉ ዋሃቢዝም ነዉ። ዋሃቢስቶች፣ እንኳን ከእስልምና ዉጭ ያሉ እምነቶችን ሊታገሱ ቀርቶ፣ ከነርሱ የቁራን አተረጓገም የተለየ አተረጓገም ዉጭ፣ ቁራንን የሚተረጉሙ ሌሎች ሙስሊሞችን ሳይቀር አይቀበሉም። ከነርሱ አመለካከትና እምነት ዉጭ ያሉ የሌላ እምነት ተከታዮች በሙሉ፣   እነርሱ ትክክለኛ ወደሚሉት እስልምና ካልመጡ በቀር «መጥፋት አለባቸው» ብለዉ የሚያምኑ ናቸዉ።

ሳዉዲ አረቢያ፣  የእስልምና ሁለቱ ታላላቅ ከተሞች (መካና መዲና) ያሉባት አገር ናት። የሳዉዲ ሙፍቲም፣ ፖፑ ለካቶሊኮች እንደሆኑት፣  ለሱኒ ሙስሊሞች መንፈሳዊ አባት ናቸው። በቅርቡ እኝህ ዋሃቢስቱ የሳዉዲ አረቢያዉ ሙፍቲ የተናገሩት፣ ስለዋሃቢዝም ምንነት በግልጽ የሚያመላክት ነዉ። «በአካባቢያችን  ቤተ ክርስቲያን መሰራት የለበትም። የተሰራም ካለ ደግሞ  መፍረስ በማለት ነበር ከዋሃቢዝም እስልምና ዉጭ ሌላ እምነትን ማስተናገድ እንደማይችል በግልጽ ያሳወቁት።

ከሁለት አመታት በፊት በወጣቶች እንቅስቃሴ የተነሳዉ የግብጽ አብዮት፣  ሙባረክ ከስልጣን እንዲነሱ አደረገ። ዋሃቢዝምን መመሪያዉ ያደረገዉ  የሙስሊም ወንድማማቾች ድርጅት፣ በየመስኪዶቹ ስለተደራጀ በቀላሉ ምርጫዉን አሸነፈ። ሞርሲ የአገሪቷ ፕሬዘዳንት ሆኑ። አዲስ ሕገ መንግስት የመጻፍ ስራ ተጀመረ። ሕገ መንግስቱ ከሻሪያ ጋር የተገናኘ እንዲሆን ተደርጎ ተዘጋጀ። ክርስቲያኖችና  አክራሪ ያልሆኑ ሙስሊሞች ተቃወሙ። ሞርሲ ግን እስልምናን  የበላይ የሚያደርግ፣ ለሌሎች እምነቶች እውቅና የማይሰጥ ሕገ መንግስት አስጸደቁ። ቁጥራቸው እጅግ በጣም ብዙ የሆኑ ክርስቲያኖች ባሉባት ግብጽ፣ የእስላማዊ መንግስት ተቋቋመ። ከሙባረክ አምባገነንነት ግብጽ ወደ እስልምና አክራሪነት ተሸጋገረች። የበጋዉ አብዮት ወደ ክረምት ጭጋግ ተቀየረ። ከእሳት ወደ ረመጥ ይሉታል ይሄ ነዉ።

በኢትዮጵያ የእስልምና  መንግስት በኃይል ለማቋቋም የአጭርና ረጅም ጊዜ እቅድ አውጥተዉ፣ በሳዉዲዎችና ግብጾች ተረድተዉ፣ በነርሱም  ሰልጥነዉ፣ ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ ዋሃቢስቶች አይኖሩም ብሎ ማሰብ አስቸጋሪ ነዉ። እነዚህን አክራሪዎችን  ተከታትሎ፣ የገንዘብ ምንጫቸዉን አድርቆ፣ አክራሪነት እንዳይስፋፋ የማድረግ ሃላፊነትና ግዴታ መወጣት፣ ከማንም መንግስት የሚጠበቅ ነዉ። በዚህ ረገድ የአገሪቷን  ሕግ ተከትሎ አክራሪነትን ለመከላከል የሚደረግ ማናቸዉም አይነት እርምጃን  አልቃወምም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቁም ነገር ተናጋሪ የሌለበት መንግስት……

ነገር ግን አክራሪነትን ለመዋጋት በሚል ሽፋን፣ የበለጠ አክራሪነትን የሚያስፋፋ፣ ለአገር የማይጠቅም፣ የአገሪቷን ሕግ የማያከብር ተግባራትን  መፈጸም ግን፣  እያንዳንዱን  ዜጋ ሊያሳስብና ሊያስቆጣ የሚገባ ነዉ።

በአገራችን በሙስሊሞች መካከል በተፈጠረው ችግር አማካኝነት፣  የተወሰኑ ወገኖች በሽብርተኝነት ክስ መታሰራቸዉ ይታወቃል።  የነዚህን ወገኖችን መታሰር ተከትሎ ፣ ከዚህ በፊት ለአንባቢያን ባቀረብኩት ጽሑፍ ፣ የሚከተለዉን  ምክር ለኢሕአዴግ አመራር አባላት አቅርቤ ነበር

«በመስኪዶች ሰላማዊ ተቃዉሞ ማሰማት፤ የመጅሊስ አመራሮች እንዲለወጡ መጠየቅ «ሽብርተኛ» ሊያሰኝ አይገባም። በመሆኑም ከሳዉዲ አረቢያ ጋር ግንኙነት የሌላቸው፣ የዋሃቢዝም አክራሪነትን ማስፋፋታቸዉን የሚያሳይ መረጃ ያልተገኘባቸዉ፣ በአዋሊያና በመስኪዶች ሕገ መንግስቱ የሚፈቅድላቸዉን  ተቃዉሞ በማሰማታቸው ብቻ የታሰሩ፣ ሰላማዊ ሙስሊም ወገኖቻችን ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ መፈታት አለባቸው። እነርሱን በማሰር የሚገኝ አንዳች ጥቅም የለም። ዜጎች ተቃዉሞ ስላሰሙ የሚታሰሩበት አሰራር መቆም አለበት። ኢሕአዴግ በዚህ አንጻር ከኃይል እርምጃዎች ተቆጥቦ ማስተዋል ያለበት እርምጃ እንዲወስድ እመክራለሁ»

በቅርቡ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን አንድ ዘገባ አቀረበ። የቀረበው ዘገባ፣  የኢቲቪ ሪፖርተሮች፣ በታሰሩ ወገኖች ላይ የቀረበዉን  የፍርድ ቤት ሂደት ተከታትለው የዘገቡት ዘገባ አልነበረም። በፍርድ ቤት የቀረቡ ሰነዶችን አላነበቡም። ፍርድ ቤቱ የሰጠዉን ውሳኔ አልገለጹም። ነገር ግን እጆቻቸው በካቴና ከታሰሩ እስረኞች ጋር፣  በእሥር ቤት የተደረጉ ቃለ ምልልሶችን ነዉ ያቀረቡት።

እስረኞቹ ለተጠየቁት ጥያቄ ምላሽ ይሰጣሉ። አስቀድሞ ተጽፎ እንዲናገሩ የተሰጣቸው  ይሁን እዉነቱን  ለማረጋገጥ አይቻልም። በመሆኑም እስረኞቹ የተናገሩትን ይዘን፣  «እንዲህ ነዉ» ወይም «እንደዚያ ነዉ»  ልንል አንችልም።

ይልቅስ ብዙዎቻችንን  ያሳሰበና ያሳዘነ  ጉዳይ ቢኖር እስረኞቹ በመጀመሪያ ደረጃ በቴሌቭዥን እንዲናገሩ መደረጉ ነዉ። ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ባለበት ወቅት፣  አስቀድሞ በፍርድ ቤት ሊቀርብ የሚገባን  ነገር በሜዲያ ማዉጣት፣  ሂደቱን የፍርድ ሂደት ሳይሆን የፖለቲካ ሂደት አድርጎታል።

የአገሪቷ ሕገ መንግስት ፍርድ ቤቶች  ነጻ እንደሆኑ ይደነግጋል። ነገር ግን ኢቲቪ ያቀረበዉ ፕሮግራም በቀጥታ የፍርድ ሥርዓቱን የሚንድ ሆኖ ነዉ የተገኘዉ። የዜጎችን ሕገ መንግስታዊ መብቶች የሚጋፋ፣ ፍርድ ቤት ዉሳኔ ሳይሰጥ በፍርድ ቤት ሥራ ላይ ጣልቃ የሚገባ ጎጂ ተግባር ነዉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከማይቀር ታሪካዊ ስህተት እና ክህደት ራሳችን እና አገራችን እንታደግ !

የታሰሩ ወገኖች ጥፋተኛ ይሁኑ አይሁኑ ገና ፍርድ ቤት አልወሰነም። ፍርድ ቤት እስካልወሰነ ድረስ ማንም ወንጀለኛ ጥፋተኛ ተደርጎ ሊቆጠር አይችልም። ኢቲቪ እነዚህን ሰዎች አቅርቦ ኑዛዜ ማናዘዙ በሕግም ሆነ በሞራል አንጻር ተቀባይነት የሌለዉ፣  ኢሕአዴግን እንቃወማለን የሚሉ ብቻ ሳይሆን ኢሕአዴግን የሚደግፉ ሁሉ ሊያወግዙት የሚገባ ነዉ። አንድ በሉ።

እነዚህ እስረኞች በኢቲቪ ቀርበዉ ቃለ መጠይቆችን ሲሰጡ፣  ጠበቆቻቸው በአካባቢው አለመኖራቸውን መርሳት የለብንም። ሕገ መንግስቱ ዜጎች የጥብቅና መብት እንዳላቸው በግልጽ ያስቀምጣል። ዜጎች በፍርድ ቤትም ሆነ በፖሊስ ፊት ሲቀርቡ ከጠበቆቻቸው ጋር የመመካከር፣ ጠበቆቻቸውም በነርሱ ስም ምላሽ እንዲሰጡ የማድረግ ሙሉ መብት አላቸዉ። ኢቲቪ ከማረሚያ ቤት ሃላፊዎች ጋር በመነጋገር፣ ጠበቃዎቻቸዉን አልፈው፣ በአቋራጭ እስረኞችን ማናዘዛቸዉ ትልቅ ስህተት ነዉ። ሁለት በሉ።

«እስረኞቹ ቃለ መጠይቆች  ሲሰጡ በዉዴታና ነዉ ወይንስ ተገደው ?» ለሚለው ጥያቄ ግልጽ የሆነ ምላሽ ሊሰጥበት ይገባል። «እስረኞቹ ድብደባና ስቃይ ስለበዛባቸው  ነዉ ባለስልጣናቱ መስማት የሚፈልጉት የተናገሩት» የሚሉ ወገኖች አሉ። እስረኞች መደብደባቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ባይኖርም፣ አለመደብደባቸዉንም የሚያሳይ መረጃ የለም። በመሆኑም በዚህ ረገድ ኢሕአዴግ ግልጽ ምላሽ መስጠት ይጠበቅበታል። ሶስት በሉ።

እንግዲህ ከዚህ በመነሳት ነዉ፣  ኢሕአዴግን እንደግፋለን የሚሉ ወገኖች፣ በሚደግፉት ድርጅት አመራር አባላት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ የሚከተሉትን ነጥቦች የማስቀምጠዉ።

  1. በኢቲቪ የተላለፈው ፕሮግራም እንዲቀናበርና እንዲተላለፍ መመሪያ የሰጡ ባለስልጣናት፣ የማስታወቂያ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሊጠየቁ ይገባል። ኢሕአዴግ ሃላፊነት የሚሰማዉ እንደሆነ የኢሕአዴግ ደጋፊዎች ሲናገሩ እንሰማለን። እንግዲህ ሃላፊነት ከሚሰማዉ ድርጅት የሚጠበቀዉ ለተሰሩት ስህተቶችና ጥፋቶች የአመራር አባላቱ ተጠያቂ ሲሆኑ ነዉ።
  2. የታሰሩ እስረኞች  በኢቲቪ ሆነ፣ ጠበቆቻቸው በሌሉበት፣ የተናገሩት ሁሉ በፍርድ ቤት እንደ መረጃ እንዳይቀርብ፣  ከጠበቆቻቸው ጋር ያለ አንዳች ገደብ እስረኞቹ መገናኘት እንዲችሉ መደረግ አለበት።
  3. ከሳዉዲ አረቢያ ጋር ግንኙነት የሌላቸው፣ የዋሃቢዝም አክራሪነትን ማስፋፋታቸዉን የሚያሳይ መረጃ ያልተገኘባቸዉ፣ በአዋሊያና በመስኪዶች ሕገ መንግስቱ የሚፈቅድላቸዉን  ተቃዉሞ በማሰማታቸው ብቻ የታሰሩ፣ ሰላማዊ ሙስሊም ወገኖቻችን ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱና ያሉት ችግሮች በሙስሊሞቹ  በራሳቸው እንዲፈታ ማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ መፈጠር አለበት። ቅንነት ያለበት ንግግር ብቻ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ የሚሰጠዉ።
ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሦስት ጊዜ በላይ የሞተ ብቸኛው ዝነኛ የሀገር መሪ

ዜጎችን በማሰር፣ ዜጎችን  በቴሌቭዥኝ በማዋረድና በማሳነስ አገር አትለማም። ዜጎች ጥፋተኛም  ቢሆኑ የሰብአዊ መብታቸው ሊከበር ይገባል። የኢሕአዴግ ደጋፊዎች፣ ከኢሕአዴግ አመራሮች መመሪያ ተቀብለው፣  የሚደግፉት ድርጅታቸው በሚያደርጋቸው መልካም የልማት ተግባራት እንድንተባበር እንደሚገፋፉን ሁሉ፣ ድርጅታቸው የሚያደርጋቸውን ጎጂና አሳዛኝ የሰብአዊ መብት ረገጣን በአስቸኳይ እንዲያቆም በመጠየቅ፣  በአመራር አባላቱ ላይ ግፊት እንዲያደርጉ በአክብሮት እጠይቃለሁ።

በዚህ አጋጣሚ የኢቲቪን አሳዛኝ ዘገባ እንደመሳሪያ በመጠቀም፣ ጉዳዩ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ሳይሆን የሃይማኖት ጉዳይ እንደሆነ ለማቅረብ የምንሞክር ካለን፣  ጥንቃቄ ብናደርግ ጥሩ ነዉ እላለሁ። በሃይማኖት ጉዳይ ላይ «እንደዚህ ነዉ እንዲዚያ ነዉ» ብሎ፣  ለጊዚያዊ ትንሽ የፖለቲካ ትርፍ ብለን፣ የሚገነባ፣ የሚያስታርቅና የሚያቀራርብ ሳይሆን፣  ነገሮች የበለጠ ወደ ከረረ ሁኔታ የሚወስድ እንቅስቃሴ ባናደርግ መልካም ነዉ። ከገዢዉ ፓርቲ ጋር ችግር ስላለን ብቻ፣ ከተቀጣጠለ ሊበርድ የማይችልን እሳት ባንለኩስ ይሻላል።

ኢሕአዴግን የምንቃወምበትና የምናወግዝበት ብዙ የተጨበጡ ምክንያቶች አሉ። እስከሚገባኝ ድረስ ግን ላለፉት 20 አመታት ኢሕአዴግ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ መልካም በማድረግ እንጂ የእምነት ነጻነትን በመጋፋት አይታማም። ኢሕአዴግ የሃይማኖት ነጻነትን የተጋፋ አይመስለኝም። በኢሕአዴግ ዘመን፣ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ነው መስኪዶችን የገነባዉ። ከሃያ አመታት በፊትና እና አሁን በአዲስ አበባ ብቻ ያሉትን የመስኪዶች ቁጥር ማወዳደሩ ብቻ ይበቃል። ሙስሊሞች በታላቁ ስታዲየም በፈለጉበት ወቅት ተሰባስበዉ ለመስገድና ለመጸለይ የተከለከሉበት ጊዜ የለም። የፈረሱ፣  የተቃጠሉ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት እንዳሉት፣ የተዘጋ ፣ የፈረሰ ወይንም የተቃጠለ አንድም መስኪድ የለም። ተቃዉሞዎች ስናቀርብ፣ በተቻለ መጠን እዉነትን ይዘን ብንቃወም ጥሩ ነዉ።

በነገራችን ላይ ፣ ኢቲቪ ያቀረበዉ አሳዛኝ ድራማ በሙስሊሙ እስረኞች የተጀመረ አይደለም። ከዚህ በፊትም አኬልዳማ የተሰኘ አሳዛኝ ድራማ ቀርቦ እንደነበረ መዘንጋት የለብንም። ስለዚህ ሃይማኖትን ከዚህ እናዉጣ። ጥያቄዉ የሃይማኖት ጥያቄ አይደለም። ጥያቄዉ የሕግ፣ የሞራልና የሰብዓዊ መብት ጥያቄ ነዉ።

 

4 Comments

  1. በድጋሜ ይድረስ ለአማኑኤል ዘሰላም! ከዚህ በፊት ethiopia zare በሚለው ድረ ገጽ ስለ እስልምና እና ወቅታዊ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል የጻፍከውን ሃሳብ ሳነብ ፤ አውቀህም ይሁን ባለማወቅ ብዙ የተዛቡ ሃሳቦችን በማገኘቴ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት የመተራረም ባህል መሰረት በ ድረ ገጹ አድሬስ እና በግልህ አድሬስህ ሊታረሙ የሚገባቸውን ጉዳዮች በላኩልህ መሰረት በሃሳቤ እንደተስማማህበት አጭር መልእክት ልከህልኝ ዝርዝሩን እንደምትልክልኝ ቃል ከገባህ በኋል ሳትልክልኝ ይሄውና አሁን ደግሞ በዚህ ድረ ገጽ ተገናኘን።
    ያም ሆነ ይህ እንደኔ እምነት ከሆነ ማንም ሰው ስለ አንድ ነገር ሃሳቡን ቢገልጽ እሰዮው ነው። ነገር ግን የሚተላለፈው ሃሳብ እውነታ ላይ የተመረኮዘ መሆን ይገባዋል ባይ ነኝ። ከሂህ ቀደም በለቀቅከው ጽሁፍ ውስጥ ስህተት ናቸው ብዬ እንደተቸሁት ሁሉ አሁንም በዚህ ጽሁፍ ውስጥ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ትክክለኛ ሳይሆኑ የተጠቀሱ ሃሳቦችን ወይም ደግሞ የተጋነኑ ሃሳቦችን ከዚህ በታች ባጭሩ ለመዘርዘር እሞክራለሁ።
    <> የሚለው ሃሳብህ ስህተት እንደሆነ ይሰማኛል። እንደውነቱ ከሆነ አንድ እየሱስ ጌታ ነው ብሎ የሚያስቀምጥን ቅዱስ መጽሃፍ ሃሳብ አንድ ሰው ትርጉሙን በማዛባት ተርጉሞ ሲናገረው የዚያ ሃይማኖት ተከታይ ሰው ስህተት ነው አልቀበልም ቢል ክፋቱ እምኑ ላይ ነው? የማንኛውም ሃይማኖት ተከታይ አምኖበት የተከተለውን ሃይማኖት ከማንም በላይ እውነት ነው ብሎ ስለሚያምን ያንን ሃይማኖቱን ትክክል ነው ተቀበሉት ብሎ ያስተምራል፤እንዳይዛባም ይከራከራል። ይሄ በራሱ ችግር አይመስለኝም። ችግር የሚሆነው እኔ የተከተልኩትን ሃይማኖት ታልተከተልክ አጠፋሃለሁ የሚል ሃሳብ ካለ ነው። ይህ ደሞ በቁርአን ፈጽሞ የተከለከለ ነው።
    ስለምን ነው እኛን ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን አንድ ጊዜ ከሳውድ ሌላ ጊዜ ከአፍጋኒስታን በማዛመድ ጥላሸት ለመቀባት የምትሞክሩት።እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ከሳውድ ወይም ከሌላ የሙስሊም አገር መጥቶ ተቋም መስርቶ ኢትዮጵያዊ ሙስሊሞችን እየረዳ ወይም እያስተማረ ያለ እዚህ ግባ የሚባል ድርጅት በተጨባጭ አለን? በእርግጥ መንግስትስ እንድህ አይነቱን ድርጊት ይፈቅዳልን? እኔ ሁሌ ከሚቆረቁረኝ ነገር በለለ ነገር ላይ ተጋኖ የሚቀርብ ሃሳብ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ከየትኛውም አገር የተሻለ የሃይማኖት ሊቃውንት ስላሉ የውጭ ተጽኖን የሚሻ ማንም የለም። ነገር ግን አንድ በሚያደርጉን ሃይማኖታዊ እሴቶች ላይ ከማንኛውም አገር ጋር ጤናማ የሆን ግንኙነት ማድረጋችን ግድ ይላል። ለምሳሌ አንድ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ሳውድ ሂዶ ሃጅ አድርጎ መምጣቱ ወይም ደግሞ የትኛውም አገር እሚገኝ ሃይማኖታዊ ተቋም ውስጥ ሂዶ የሃይማኖት ትምህርቱን ቢያጠና የተለየ ትርጉም ሊሰጠው አይገባም።
    ሌላውና ሳልፈልገው ለመጥቀስ የምገደደው ነገር የምእራባዊያን አገሮች ድምጻቸውን አጥፍተው በግብረ ሰናይ ድርጅት ስም እንደ ሰደድ እሳት እያስፋፉት ያለው አንዱን አግልሎ ሌላውን የሚያቀርበው ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴያቸው ለምን አይነሳም? አሁን ስልጣናቸውን መከታ አድርገው ለስራ ጉዳይ በማስመሰል በአበልና በመንግስት መኪና እንደፈለጉ በተለያዩ ክልሎች እየዞሩ ሃይማኖታቸውን የሚሰብኩትስ ቱባ ባለስልጣኖች ለምን አይተቹም? የቤኒ ሻንጉል ክልል ፕረዚዳንት የነበሩት አቶ ያረጋል አይሸሹም ከምእራባዊያን ጋር በመመሳጠር በስልጣን ዘመናቸው ብቻ ያሰሯቸው 500 ቤተ እምነቶችስ ለምን አድስ አበባ በኢሃድግ ዘመን ሙሉ ተሰሩ ከተባሉት መስግዶች ጋር አብረው አይተቹም?
    በዚህ ጽሁፍ ላይ ያየሁት ወይም ተጋኖ የቀረበ ሃሳብ ኢሃድግ ለሙስሊሙ ከሌላው ሃይማኖት ተከታይ በተለየ ነጻነት የሰጠ መሆኑን የሚያብራራው ሃሳብ ነው። በእርግጥ ከአጼወቹ ጋር ታነጣጠርነው ይሄ ሃሳብ እውነት ሊመስለን ይችል ይሆናል። ሆኖም ግን በእኔ እምነት ይህ ሃሳብ ስህተት እንደሆነ ይሰማኛል። ጠለቅ ብለን ታየነው አሁን ኢሃድግ በሙስሊሙ ላይ እያደረገ ያለው አክራሪወቹ አጼወች ከፈጸሙት የባሰ ጭቆና ነው። አጼወቹ ሲሉ የነበሩት እኔ የምከተለው ሃይማኖት ትክክል ስለሆነ ይህንኑ ተከተሉ ነበር። አሁን ግን እየሆነ ያለው ከዚህ የከፋ ነው። ልብ በሉ! ሃገራችን ከሳውድ አረቢያ ቀጥላ እስልምና ሃይማኖትን ከስር ከመሰረቱ አቅፋ ያሳደገች እንደመሆኗ መጠን እጅግ በጣም ጥልቅ እውቀት ያላቸው አባቶች ሞልተውናል። ታዳ በምን ሂሳብ ነው እኝህ መከራ ስቃያቸውን እያዩ ሃይማኖቱን ሲንከባከቡና ሲያስተምሩ የነበሩ ብርቅየ አባቶች እየተገፉ በቦታቸው ምንም የሃይማኖቱ ግንዛቤ የለላቸው ወሮበሎች እንደ ሃይማኖት መሪ የሚመደቡት? ለምንስ ነው የረዥም ጊዜ ልምድና እውቀት ያላቸው ኢትዮጵያዊ አባቶች እያሉ ከውጭ ሃገር መጤወችን አስመጥቶ በአስተርጓሚ ህዝቡ የሃይማኖቱ አስተምህሮ ክፍል ያልሆነን ስልጠና እንድወስድ የመደረገው? አሁን ኢሃድግ እያደረገ ያለው ፈጣሪያችን በመጽሃፉ ያስቀመጠልንን ትተን እሱን እንድናምን እና እንድናመልክ እያስገደደን ነው። እንድህ አይነቱ መንግስታዊ ሃይማኖት በሃገራችን ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ታሪካዊ ስህተት ነው። ከሊባኖስ ያመጡትን መጤ እምነት ትክክል ነውና የግድ ተከተሉ ብሎ ማሰርና መግደል በምን መልኩ ነው ትክክል ሊሆን የሚችለው? የሃይማኖት መሪወቻችን በእምነት ቤታችን በነጻነት እንምረጥ፣የተጠናከረ ተቋም ይኑረን፣ጥፋተኞች በህግ ይጠየቁ ባልን ለምን ሞትና እስራት፤ስቃይና መከራ ይወርድብናል? ታዳ እውነታው እንደዚህ ሆኖ ሳለ <> ብሎ መጻፍ ትክክል ነውን? መስጂዶች በኢሃድግ ከዚህ በፊት ከነበሩት መንግስታት በተሻለ ስለጨመሩ ስንት ግፍና መከራ እያበላን ያለውን ኢሃድግን ፍትሃዊ አድርጎ ማቅረቡ ተገቢ ነውን? ሌሎች በሃገራችን ያሉ እህት ሃይማኖቶች ከቤተ እምነት ግንባታ ባለፈ መጠነ ሰፊ የሆኑ ገቢ ሊያስገኙ የሚችሉ ተቋማት እና ብዙ ኮሌጆች የሏቸውምን? ለመሆኑ አጼወቹንም ሆነ ደርግን ለመጣል ስንታገል የነበረው ለተሻለ እንጅ ባለንበት ለመቀጠል ነው እንደ?
    በሚገርም ሁኔታ ስለሙስሊሞች የመብት መከበር የተጠቀሰው አንዱ ሃሳብ በስታዲየም በነጻነት መስገድ መቻላችን ነው። በእርግጥ እንደዚህ አይነት ኋላቀር አመለካካከትን በ21ኛው ክህለዘመን ላይ አንስቶ እንዴ መብት መከበር ማቅረብ ተገቢ ነውን? ሌላው የተነገረን የፈራረሱ እና የተቃጠሉ አቢያተክርስቲያናት እንጅ መስጅዶች አለመኖራቸውን ነው። እኔ በበኩሌ መስጅዶችም አቢያተክርስቲናትም መቃጠላቸውን በ ቪኦኤ ሳይቀር በዜና ሰምቻለሁ። አሁንም ኢሃድግ ብዙ መስጅዶችን በዶዘር እያፈረሰ እነደሆነ ኗሪወች ከተለያየ ቦታ ቅሬታቸውን እያሰሙ ስለመሆናቸው እየሰማን ነው። ያም ሆነ ይህ የእምነት ቦታወችን ማፍለስ የኢሃድግና የተላላኪወቹ ሴራ እንጅ የ ጨዋው ኢትዮጵያ ህዝብ አቋም እንዳልሆነ በድፍረት መናገር እችላለሁ። ይህን የቆየ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ጥሶ እንደዚህ አይነት ርካሽ ተግባር የሚሰራም ካለ በኢሃድግ ተራ ውንጀላ እና የተጭበረበር ክስ ሳይሆን በትክክለኛ ክስ ላይ ተመስርቶ ፍርዱን ማገኘት እንዳለበት አምናለሁ።
    ኢትዮጵያን እና ህዝቧን አላህ ከግፈኞች ይጠብቃቸው!!! አሚን።

  2. The comment of Amanuel is either biased or lacks some facts .
    You can’t label a person by his education or by source where he got his knowledge
    from ,rather it is by his belief (ideology) or by association whom he supports Amanuel has no info as how many Mosques were burnt in various regions in different times so he tried to portray the one side damage so his comment is unbalanced & misguiding .
    Otherwise as he put it Ethiopian Muslims demand is a just & human right issues not only for religious freedom .We should support without division for the sake of humanity otherwise we ,as a nation ,will pay heavy price turn by turn .
    May Almighty God Bless Ethiopia & its people

  3. Mr Zelalelm sounds very much like ETV. If you don’t believe me, take out the tittle and the last sentence and you will find that every thing he says is what is said in different tone edited with music and picture back ground in “Jihadawi Harekat”

    I also ask Why Zelalem uses different tittles for the same article posted at different web sites. For example this same article is posted in Ethiopian Review as :
    የወያኔ አክራሪነትን ለመዋጋት በሚል ሽፋን የበለጠ አክራሪነትን የሚያስፋፋ ድርጊት

    Last but not least, why did he use a tittle which has nothing to do with the body of the article? appearing to oppose the actions of woyane but by large agreeing with every thing they do. In fact, his article is very much the same as that of the “Dr …”,Interior Minister’s statement in the EPRDF drama..

    Abdella, you may wish to get a genuine response, but, I have a gut feeling and i have provided some evidences to show that he is “Awko yetegna….” I rather suggest that you write a response in Amharic so that his venomous effort won’t attack any one.Unfortunately, I can’t type in Amharic, I would have discredited each and every sentence Mr Zelalalem wrote.

    Just for points to mention: What dergue did to muslims: changed the constitution to a secular one, 3 national holidays recognized, made the playing field equal by taking away 1/3 rd of the land owned by the church, Gave equal recognition to the Muslim leaders to that of Orthodox church leaders, Allowed the establishment of the independent Islamic council (Majlis) making the most charismatic, knowledgeable (one who translated Quran to amharic) and well respected leader Shiek Mohammod Sani habit as its leader. (compare the current corrupt, ignorant appointed cadres), Relevant to the current crisis, Dergue helped the growth of Awolia school and its associated social services by providing the current land for the school and mosque and by providing financial and administrative assistance, .Does that mean dergue was good?not at all. It was a barbaric govt, which was good at distribtin oppression and poverty equally.

    About torched mosques, I agree with Abdella as to what needs to be done for these kind of criminals. To support Abdellas point, here is the link about ten torched mosques in Gurage sZone and Addiis. http://amalethiopia.wordpress.com/2010/12/09/ethiopian-orthodox-church-goers-torched-eight-mosques-gurage-zone/
    http://amalethiopia.wordpress.com/2011/01/09/mosque-burned-to-the-ground-in-addis-ababa/

    About booming mosques, what you say about booming churches? 1000 in Benshangul in few years, here is the link:
    http://www.christianactivities.com/1000-new-churches-ethiopia-africa

    I have also checked and found out that you have completely lied about Egypts new Constitution because you thought it will make your story nice.According to VOA report, it actualy significantly secular that the previous constitution. Mr Amanuel, I would have to remind you that Muslim brother hood is in power because they are democratically elected. Unfortunately, Democracy doesn’t necessarily give you what you want, rather than what the majority want. All what we need to do to get rid of the fear about Islamic state in Ethiopia is to make sure that a democratically elected govt is in place. Rest assured that the rest will fall in its right place.

    I wiould like to conclude by stating that Fundamentalism and extremism which is besieging most religions need to be tackled in a very transparent, rational thoughtful, collaborative and legal way. Any other attempt to impose a certain sect b/s the govt feels like it is the worst form of conteempt Ethiopian Muslims have ever suffered under any form of govt so far. To make it relevant for you, How would you take it if EPRFD, decides that all current Orthodox churches need to be handed over to protestants who are more “moderate” than he former? Would you feel insulted? What would you say if you govt imprisons tortures and kills, you because you have peacefully opposed such an action? I leave the judgement to you.

  4. ይድረስ ለተከበሩ አማኑኤል ዘሰላም
    እውነተኛ መረጃ ሳይኖር በጥርጣሬ ብቻ ተመርኩዘው ለንባብ ማቅረብ ያሳፍራል ይህንንም ከእርስዎ ከጻፉት በመረጃ ልጥቀስ መልስ ልስጠዎት
    1ኛ. ስለ ሳውዲ አረቢያ ውሀቢይ “ምንጩ ሳዉዲ አረቢያ ዋሃቢስቶች፣ እንኳን ከእስልምና ዉጭ ያሉ እምነቶችን ሊታገሱ ቀርቶ፣ ከነርሱ የቁራአን አተረጓገም ዉጭ፣ ቁራአንን የሚተረጉሙ ሌሎች ሙስሊሞችን ሳይቀር አይቀበሉም። ከነርሱ አመለካከትና እምነት ዉጭ ያሉ የሌላ እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እነርሱ ትክክለኛ ወደሚሉት እስልምና ካልመጡ በቀር «መጥፋት አለባቸው» ብለዉ የሚያምኑ ናቸዉ።
    ይድረስ ለተከበሩ አማኑኤል ዘሰላም
    ሳውዲ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የክርስትናና የሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች እንዳሉ ያውቃሉ?? እነ ነብዮ ሲራክ ብዙም ጽፈዋልና መጠየቅ ይችላሉ ወይም ጽሁፋቸውን ፈልገው ያንብቡ ::
    2ኛ. ስለግብጽ የሚከተለውን አስነብበውናል “የሙስሊም ወንድማማቾች ድርጅት፣ በየመስኪዶቹ ስለተደራጀ በቀላሉ ምርጫዉን አሸነፈ። ሞርሲ የአገሪቷ ፕሬዘዳንት ሆኑ። አዲስ ሕገ መንግስት የመጻፍ ስራ ተጀመረ። ሕገ መንግስቱ ከሻሪያ ጋር የተገናኘ እንዲሆን ተደርጎ ተዘጋጀ። ክርስቲያኖችና አክራሪ ያልሆኑ ሙስሊሞች ተቃወሙ። ሞርሲ ግን እስልምናን የበላይ የሚያደርግ፣ ለሌሎች እምነቶች እውቅና የማይሰጥ ሕገ መንግስት አስጸደቁ። ቁጥራቸው እጅግ በጣም ብዙ የሆኑ ክርስቲያኖች ባሉባት ግብጽ፣ የእስላማዊ መንግስት ተቋቋመ። ከሙባረክ አምባገነንነት ግብጽ ወደ እስልምና አክራሪነት ተሸጋገረች። የበጋዉ አብዮት ወደ ክረምት ጭጋግ ተቀየረ። ከእሳት ወደ ረመጥ ይሉታል ይሄ ነዉ።
    ስለ ግብጽ አዲስ ሕገ መንግስትም ጉዳይ መጀመሪያ ቢያነቡት ጥሩ ነው ካነበቡት በኋላ ደግሞ እርግጠኛ ከአለም አንደኛ ህገ መንግስት እንደሚያደርጉት አንዳችም ጥርጥር የለኝም:: ይሄ ህገ መንግስትም ለሀገራችን ቢሆን የሚመርጡት እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ:: ከሸሪዓ ህግ ጋር ምንም ተዛማጅ አይደለም የሸሪዓ ህግ ምን ዓይነት ህግ እንደሆነ የሚያውቁት አይመስለኝም የሰርቀን እጅ መቁረጥና የገደለን መግደል ባቻ አይደለም ብዙና ሰፊ የሆነ ችግሮችን የሚፈታና የሚያቃልል ህግ ነው ያም ሆነ ይህ እርስዎ በዲሞክራሲ አሰራር የሚያምኑ ከሆነ እንኳን እስልምናን አይደለም ሰንጣኒዝም በግልጽና በዲሞክራሲዊ መንገድ ከተመረጠ የመቀበል ግዴታ አለበዎት:: አጋፋሪ ነኝ

Comments are closed.

Share