ግልጽ መልእክት ለአገራችን የታሪክ ፀሃፊዎችና ፖለቲከኞች! – (ክፍል 2)

ግልጽ መልእክት ለአገራችን የታሪክ ፀሃፊዎችና ፖለቲከኞች !
                                                               የታሪክ ተወቃሽነቱን በራሳችን እንጀምር !
                                                                                       (ክፍል 2)
                                                                                                                                                በመንገሻ ሊበን
 
   በዚህ ፅሁፍ የመጀመርያ ክፍል ላይ ፣ ባለፍ ገደም ከተፃፉ ተራ ዘለፋዎች ባሻገር ፣ የብዙ አንባቢዎችን ገንቢ ነቀፌታና አስተያየት ተቀብያለሁ ። በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም አስተያየት ሰጭዎችና ነቀፌታ አቅራቢዎች ያለኝን ልባዊ አክብሮት እየገለፅኩ በቀጥታ ወደ ጀመርኩት ርእሰ ጉዳይ አመራለሁ ።
   “ የታሪክ ተወቃሽነቱን በራሳችን እንጀምር ” በሚል ርእስ ስር በተከታታይ ክፍሎች የማቀርበው ይህ ጽሁፍ፣ በማንኛውም ወገን ላይ የተነጣጠረ ጥቃት አለመሆኑን ሁሉም አንባቢዎች እንዲገነዘቡልኝ እወዳለሁ ። የፅሁፉ ዋነኛ አላማ “በሃገር ደህንነት ስም” ወይም በሌላ ሽፋን ፣ ከህዝባችን የተደበቁና በታሪክ ፀሃፊዎቻችንና ፖለቲከኞቻችን ብእሮች እምብዛም ያልተዳሰሱ ታሪኮች ይፋ ወጥተው ትውልድ ይማርባቸው ዘንድ እንዲተጉ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን አካላት ማሳስብና ማስገንዘብ ነው።
 
   እርግጥ ነው በቀዳሚው ፅሁፌ መግቢያ ላይ እንዳልኩት ካሁን በፊት ከተፃፉልንና ካነበብናቸው “ወገንተኛ” አልያም “የተዛነፉ” ታሪክ ቀመስ መጣጥፎች አኳያ…በዚህ ርዕስ ስር በንዑስ አቅም የሚቀርቡ ጭብጦች ፣ እንደ እሬት የሚመረን በርካታ ሰዎች መኖራችን የሚጠበቅ ነገር ነው። ይሁን እንጅ የራሳችን ታሪክ የራሳችን ነውና ወደድንም ጠላንም ልንቀበለው የግድ ይለናል !!
 
      ከተወሰኑ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የአመራር አባላት ጋር በተለያየ አጋጣሚ አብሬ የሰራሁ ሰው እንደመሆኔ መጠን ፣ አብዛኛዎቹ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የአመራር አባላት ፣ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ታሪክ ላይ ፣ በተለይም ደግሞ በኤርትራ ጉዳይ ላይ ያላቸውን አቋም በቅርበት የማወቅ እድሉን አግኝቻለሁ ፣፣ በእርግጥ አንዳንድ መሪዎቻችን ለአገራችን ካላቸው ጥልቅ ፍቅር አኳያ፣ የኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠል በእጅጉ እንደሚያንገበግባቸው ጠንቅቄ ባውቅም …አብዛኛዎቹ መሪዎቻችን ግን በተቃራኒው ፣ የኤርትራን ጉዳይ በተለይም ደግሞ የአሰብን ጉዳይ ከአምባገነኑ የወያኔ መንግስት ጋር ለሚያደርጉት ትንቅንቅ ፣ የህዝባችንን ቀልብ ለመሳብ ሲሉ ብቻ “እንደመጫዎቻ ካርታነት” እንደሚጠቀሙበት አሳምሬ አውቃለሁ። (“አሰብ የማን ነች” በሚል ርእስ ስር ከዓመታት በፊት ታትሞ ለንባብ በበቃው የዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም መፅሃፍ ላይ የቀረቡትን የተዛነፉና የተንጋደዱ ታሪኮችን ልብ ይሏል ። በዚሁ መፃህፍ ላይ የአሰብን ኢትዮጵያዊነት ለማሳመን እንደማስረጃነት የቀረበው የደርግ የራስገዝ ሽንሸና የዶክተሩን “ብስለትአልባ ፖለቲከኝነት” ወይም “አውቆ አጥፊነት” ያሳበቀ ይመስለኛል።ለማንኛውም በዚህ ጉዳይ ላይ ለወደፊቱ ሰፋ ያሉና በማስረጃ ላይ የተደገፉ ፅሁፎችን ለማቅረብ እሞክራለሁ ።
 
     በመሰረቱ እኔ ለኤርትራና ህዝቧ ጥብቅና የመቆም ሃሳብም ምኞትም የለኝም ። ይልቁንም እንደ አንድ አገሩን የሚወድ ኢትዮጵያዊ መጠን የኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ መገንጠል በእጅጉ ያንገበግበኛል ። የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝቦች የመጨረሻ እድል በእንዲህ አይነቱ አሳዛኝ ድምዳሜ መቋጨቱም እጅጉን ያሳዝነኛል ።
 
      ነገር ግን ፣ የኤርትራን ህዝብ ከኢትዮጵያ ለመገንጠል ያበቃው ዋነኛ ምክንያት ምንድን ነው በእውን ይህ ህዝብ ከኢትዮጵያ ለመገንጠል የወሰነው ፣ አብዛኛዎቻችን እንደምንለው “ ሻእቢያና ወያኔ ባቀነባበሩት ሴራ ብቻ ነው ” ወይስ ከኛ የተሰወረ አልያም የተዛነፈ ሌላ ታሪክ አለ…የሚለው አንኳር ነጥብ ፣ ከትላንቱ የሃቀኛ ታሪካችን ፍፃሜ አኳያ መቃኘት አለበት የሚል የፀና እምነት አለኝ ። ምክንያቱም የዚህ ታሪክ ይፋ መውጣት ፣ ለኢትዮጵያችን የወደፊት ደህንነትና አህዳዊነት የማይናቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋልና !! 
 
      ትላንትና ከትላንት ወዲያ ፣ ኤርትራን ጨምሮ በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ የተከተልነው አቋም ከእውነተኛ ፍፃሜው በታቃረነ መልኩ እንደተሸፋፈነ አልያም እንደተዛነፈ ይቀጥል ካልን ግን፣ ነገና ከነገ ወድያ የኢትዮጵያን አንድነተት ለሚፈታተኑ ከፍተኛ አደጋዎች ራስን ማጋለጥ ከመሆኑም ባሻገር የወደፊቱ ትውልድ ታሪክም እንዳሳለፍናቸው አሰቃቂ ታሪኮች ሁሉ የጦርነትና የእልቂት እንዲሆን መፍረድ ማለት ነው ። ስለዚህ “ያለፈው ይበቃል እውነተኛው ታሪካችን ሳይዛነፍና ወደ የትኛውም ወገን ሳያጋድል ይነገረን ፤ ይፃፍልን ” የምንልበት ወቅት አሁን መሆን አለበት ።
 
      አሁንም ሆነ ወደፊት ደጋግሜ ለመግለፅ የምፈልገው ነገር ቢኖር፣ የታሪክ ድርሳን ማለት አኩሪ ፍፃሜዎች ብቻ እየተመረጡ የታጨቀቡት ተራ መዝገብ አለመሆኑን ነው። ታሪክ ማለት ጣፋጭና መራራው ፤ድክመትና ጥንካሬው በአንድ ላይ ተቀይጦ የሰፈረበት የትላንት እውነተኛ ፍፃሜዎች ሰነድ ነው ። ትላንትና ከትላንት ወዲያ በአያቶቻችንና ቅድመ አያቶቻችን የተፈፀሙ ታሪኮች በሙሉ የተሳሳቱ ናቸው አልያም ደግሞ ከነበሩበት ጊዜና ዘመን አንፃር ፍፃሜዎቻቸው በሙሉ የተወገዙ ናቸው የሚል አቋም የለኝም ። ምክንያቱም አንድ አስተያየት ሰጭ እንዳሉት.. “ የአያቶቻችን ስራ የሚመዘነው በአሁኑ ዘመን ሳይሆን…. እነርሱ በነበሩበት ዘመን ነውና ” ። ይሁን እንጅ በእነርሱ የተፈፀመው የትላንቱ ታሪክ ለኛና ለልጅ ልጆቻችን ትምህርት ይሆነን ዘንድ ሳይዛነፍና ሳይንጋደድ መቅረብ አለበት የሚለው አቋሜ መቼም ቢሆን የሚቀየር አይሆንም ።
 
       በየትኛውም ዘመን የነበሩ መሪዎቻችን፣ ለአገራችን ኢትዮጵያ ያበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦና ስራ መቼም ቢሆን የሚረሳ አይደለም። ከሰሯቸው ታሪኮች መካከል ደግሞ አዎንታዊ ስራዎቻቸው ይበልጥ የጎሉ መሆናቸውን ማንም ሊክደውም አይችልም። ግን ደግሞ ታሪካቸው በሙሉ አዎንታዊ ብቻ ነበር ማለት አይደለም፤ አሉታዊ ስራዎቻቸውም የታሪካቸው አካል ነውና። የአፄ ዮሃንስን አንገት ቀንጣሽነት አልያም ደግሞ የአፄ ቴድሮስን እግርና እጅ ቆራጭነት የማያምን ኢትዮጵያዊ ካለ፣ ወደ ወሎ ፤ ወደ ጎጃም አልያም ወደ ሸዋ ጎራ ይበልና ፣ ሆን ተብለው እንዲድበሰበሱ የተደረጉ ታሪኮችን ያፈላልግ ። የአፄ ምኒልክን ጡት ዘልዛይነት ለማጣራት የሚሻ ኢትዮጵያዊ ካለም …. ወደ ኦሮምያ ክልል(አርሲጎራ ይበልና በየስፍራው የሚገኙ እድሜ ጠገብ አዛውንቶችን ይጠይቅ ። ነፍጠኛ የሚለው “የተዛነፈ” ስማችንም መነሻው ምን እንደሆነ ይመርምር ። ይህ ሁሉ ታሪክ የኛ የራሳችን ነው ። ከዚህ ያለፈ ታሪክ ነው መማር ያለብን ። ከዚህ እውነተኛ ታሪክ ስንማር ነው… በወያኔና መሰሎቹ የሚነዛውን የዘረኝነት ፕሮፓጋንዳ ያላንዳች ልዩነት በጋራ ልናመክነው የምንችለው ። ከዚህ ውጭ ግን ሁሉም በየፊናውና በየዘመኑ እየተነሳ፣ ለራሱ እንዲመቸው አድርጎ የሚነግረን የተንጋደደና የተዛነፈ ታሪክ እንዲቀጥል የምንፈቅድ ከሆነ፣ ትውልድን ያሳስታል ብቻ ሳይሆን አገራችንንም ሊያሳጣን ይችላል !!
 
        በእኔ እምነት ዛሬ በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ላለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ መሰረቱ የትላንቱ የተዛባ ታሪክ ነው ። እንደ በርካታ የትግራይ እድሜ ጠገብ አዛውንቶች አባባልና፣ እንደህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ መሪዎች እምነት፣ ለአጼ ዮሃንስ በድርቡሾች መገደልና ለትግራይ ስርወ– መንግስት ማክተም ዋነኞቹ ተጠያዎች የአማራ መሳፍንቶች ናቸው። እንደነዚህ ወገኖች እምነት ፣ የአማራ መሳፍንቶች የተለያዩ ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለድርቡሾች አሳልፈው ባይሰጡ ኖሮ…አጼ ዮሃንስ ባልተገደሉ፣ ትግራይን ማእከል ያደረገው ስርወ መንግስትም ከትግራይ ወደ ሸዋ ባልጋዘ ነበር ። ይህ እምነታቸው ነው እንግዲህ ከ100 አመታት በኋላ በአማራ ህዝብ ላይ የበቀል ሰይፍ እንዲመዙ ያበቃቸው ።እነ አቶ ስብሃት ነጋ ሳይቀር “ እንደ አያቶቻችሁ አርቀን እንቀብራችኋለን ” እያሉ የሚፎክሩብን፣ ከልጅነታቸው ጀምረው እየተጋቱት ባደጉት በዚህ የተዛባና የተንጋደደ ታሪክ ምክንያት ነው ። የኤርትራም ጉዳይ ከዚህ ተነጥሎ የሚታይ አይደለም ። በኦሮሚያና በሶማሌ አልያም በሌሎች ክልሎች አልፎ አልፎ የሚንጸባረቀው ስሜትም የዚህ መሰሉ ታሪክ አንድ ነፀብራቅ ነው ።ይህን መሰሉን ታሪክ ነው እንግዲህ “ ታሪክ እንደፀሃፊው ነው በሚል ወገንተኛ ስሜት ሳይሆን ፣ በሃቀኛና ሚዛናዊ መልኩ ግልፅ ይሁንና ፣ ሁላችንም እንማማርበት እያልኩ ያለሁት።
 
    ያም ሆነ ይህ በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ ጊዜ ከማባከንና … ለመፃፍ ከተነሳሁበት ርእሰ ጉዳይ ላለማፈንገጥ ስል፣ በእንጥልጥል ወዳቆምኩት ርእሰ ጉዳይ ልመለስ ። እንቀጥል………
 
      በኢትዮጵያና በፋሽስት ጣልያን መካከል ከተደረሱት ሶስት ስምምነቶች (190019021908) በፊትም ሆነ በኋላ ባሉት ረጅም ዓመታት ፣ ኤርትራን አሁን ባላት ቅርፅና ይዞታ ግዛቴ ናት የሚል ጥያቄ በኢትዮጵያ በኩል ስለመቅረቡ ምንም የተገኘ ማስረጃ የለም ። የፋሽስት ሰራዊት በአገራችን ላይ ያካሄደውን ሁለተኛውን ወረራ ተከትሎ በመንግስታቱ ማህበር ስብሰባ ላይ የተቃውሞ ንግግር ያስደመጡት ቀዳማዊ ሃይለስላሴም ቢሆኑ ፣ ታሪካዊ በተባለለት የዚያን ጊዜው ንግግራቸው ላይ አስረግጠው የተቃወሙት የኢትዮጵያን በግፍ መወረር ነው እንጅ ፣ የኤርትራን ለ 60 ዓመታት በጣልያን መገዛት አይደለም ። የኤርትራን መገዛት ለመቃወም ቢፈልጉ ኖሮ፣ መላዋ ኢትዮጵያ እስከምትወረር ድረስ መጠበቅ ባላስፈለጋቸው ነበር ። እንደማንኛውም ተጠቂ አካል በማንኛውም ጊዜ “ ሉዓላዊነቴ ተደፈረ ፤የሰሜኑ ግዛቴ በውጭ ሃይል ተወረረ ፤ የባህር በሬን ተነጠቅሁ” ብሎ ማወጅም በቻሉ ነበር ። ግን አላደረጉትም በመንግስታቱ ማህበር ታሪካዊ ዲስኩራቸው ላይም ስለ ኤርትራና ህዝቧ አንድም ቃል አልተነፈሱም ። ለምን……?
 
     ይህንን የተዳፈነ ታሪክ ነው ተመፃዳቂ ፖለቲከኞቻችን ፍርጥርጥ አድርገው እንዲነግሩን የምንጠይቃቸው ። ይህን የተንጋደደ ታሪክ ነው ፀሃፊዎቻችን በሰላ ብእራቸው ግልጥልጥ አድርገው እንዲከትቡልን የምንሻው ። ምክንያቱም በዚህ የተንጋደደ ታሪክ ምክንያት በሽዎች አልያም በመቶ ሽዎች ሳይሆን… በሚልዮን የሚቆጠሩ ልጆቻችንን ከሁለቱም ወገን አጥተናልና..!! እዚህ ላይ ቆም ልበልና…..መቼም ቢሆን ስለማይረዳኝ አንድ አንኳር ነጥብ ላንሳ..!
 
      እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ መጠን ፣ አገሬ ኢትዮጵያ በምንም አይነት የባእድ ሃይል ቅኝ እንዳልተገዛችና ፣ አውሮፓዊያን ወራሪዎችን ድባቅ መትታ በማባረር በአፍሪካ ብቸኛዋ የነፃነት ቀንዴል ለመሆን እንደበቃች እየተነገረኝ ያደግኩ ሰው ነኝ ። በእርግጥ ይህን ታሪክ እውነተኛ ታሪክ ነው ብዬ ልቀበለው ። ይሁን እንጅ ምንግዜም ቢሆን ሊገባኝ የማይችል ሌላ ታሪክ አለ ። ይሄውም የኤርትራ “ ክፍለ ሃገር ” ለ 400 አመታት ያህል በቅኝ ግዛት መላሸቅ ነው ። እንግዲህ ዋናውና እርስ በእርሱ የሚጣረሰው ነጥብ ያለው እዚህ ላይ ነው ።
 
      እውን ኤርትራ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ አካልነቷ የኢትዮጵያ ከሆነ… ለምን ይሆን ኢትዮጵያ አገራችን በምንም አይነት የባእድ ሃይል አልተገዛችም ብለን ለመመፃደቅ የምንሞክረው ???! የኤርትራ በባእድ ሃይል መገዛት እኛን አይመለከተንምን…የአንድ አካልህ መጎዳት ወይም መቁሰል… ሌላውን የሰውነት ክፍልህን አይመለከተውምን….? የቀይ ባህርንና የሁለቱንም ወደቦች የማያወላውል ኢትዮጵያዊነት ቋቅ እስኪለን ድረስ የሚነግሩን ፖለቲከኞቻችንና የታሪክ ፀሃፊዎቻችን ፣ ይህን እርስ በእርሱ የሚጣረስ ታሪክ ለምን ይሆን በግልፅ መንፈስ ሊያስረዱን የማይፈልጉት ..? የኢትዮጵያችንን በቅኝ ግዛት አለመያዝ በየሄድንበት በኩራት ስናውጅ… የኛ አካል የምንላት ኤርትራን የምንረሳት ለምን ይሆን…..? ስለዚህ በእኔ እምነት ከሁለቱ አንዱን እንምረጥ !! በኤርትራ የኢትዮጵያ አካልነት አምነን … “ ኢትዮጵያ በውጭ ሃይሎች ቅኝ ተገዝታለች’’ ብሎ አዲስ ታሪክ መፍጠር አንዱ ሲሆን….ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ የኢትዮጵያን በማንም የውጭ ሃይል አልተገዛችም ታሪክ ለማስቀጠል፣ ኤርትራን ለቀቅ ማድረግ ነው…!! እንደ እሬት ቢመረንም ምርጫው ይህና ይህ ብቻ ነው !! ከዚህ ውጭ ግን እርስ በእርሱ በተጣረሰ ታሪክ እየተጥመዘመዙ ለዘለቄታው መቀጠል ከቶውንም አይቻለንም !!
 
      ከጊዜ መጥበብ አንፃር እንጅ ሌላም ብዙ…እጅግ ብዙ ጥያቄዎችን መዘርዘር በተቻለ ። ይህን እርስ በርሱ የተጣረሰ ታሪክ ነው ለመጭው ትውልድ ትምህርት ይሆን ዘንድ በግልፅ እንናገረው እያልኩ ያለሁት ። ይህ ታሪክ ወደድንም ጠላንም የኛ የራሳችን ታሪክ ነው ። አዎ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ የምናገረው ነገር ቢኖር ፣ ይህ ታሪክ የኛ የራሳችን እስከሆነ ድረስ፣ ለመጭው ትውልድና ለልጅ ልጆቻችን ሰላምና እፎይታ ስንል እንደ እሬት ቢመረንም የግድ ልንውጠው ይገባናል ። እኛ ተደናግረን…ልጆቻችንም እንዲደናገሩና ተጨባጭነት በሌለው የታሪክ አዙሪት ውስጥ ገብተው እንዲዋልሉ መፍቀድ የለብንም ።
                                                                                                                                                              &n bsp;                                                   ይቀጥላል…..
                                                                                                                                                              &n bsp;                                                መንገሻ ሊበን
ማንኛውንም አስተያየትና ነቀፌታ መላክ ለሚፈልግ ግለሰብም ሆነ ድርጅት የጸሓፊው ኢመይል እንሆ ፣– mengesha.libenn@yahoo.com
ተጨማሪ ያንብቡ:  አገር በሕወሓት ቀጥተኛ አገዛዝ ስር

12 Comments

  1. endante ayinetu wisha sechow mesmat endet endemekefenge bayek-emitakerbachew tintenawoch be ewnet laye yetemeseretu behonu balikefa-gin hasetin ena kitfetin acheke lemegat sitmokir ayikebdhem-sima sil ertera megentel mikinyat ena sile atse yehonnes mot ke ande zeweg(maletim ke Amhara) hibreteseb bewetu sewoch yetesera tifat arge takerbalek-finafint ye meret til nek-este linger tarek-dessie ena wollo seyastedader yeneberew sew man endehone takalek? ye isayas afewerki wendem deja azemache solomon afewerk neber-esu min endesra takalek be wollo ena be dessie hizib layi-yehonk kirnatam nek gin-wisha-eshe Atse yehonness be gojjam ena be wollo hizib layi yeserut tifat tawikalek? gin Amharaw betifatachew seyabid ena yazung likekung sel semtehew takalek? abo ye engede leje nek-wish! i will find you-trust me-so now i know how to deal with you-wisha bisbis galla nehe!

  2. sile eretera ande neger lingerik-weye yatefunal weye enatefachewalen-yihen sil azinalew-ena ye agamew tigre mengist ahun eyastameme eshururu yilachewal mikinyatum ye deme ena ye akist ena ye agot leje bemel-neger gin ahunim “netsa” kewetu bewala ke enja ras aliweredum-sima este ye ahunun mikinyat nigeren lemin be torinet ena betenkol ke enja gar yeminetarekut? endant wisha sew echen metete chinkilat yizek merze titefalek-you just be the junior shabya Tesfay Gebre ebab! yes -either they will destroy us or we will destroy them-i do not give a damn shit for those wanna be Arab and italian slaves-and the fucken beja hammassen tribe-whose mentality is like a beast-they are a cancer to us! Listen i am happy that they depart from us-what i do not like is that meles gave them what is not theirs-that is the whole costline of Afar people-other wise i am happy they sceced=ke manim kirnatam gar men ore ayasefeligem!

  3. This website is owned and administered by Shabyas. There is a lot of proof.
    1. They will delete the comments if they think it is against Eritrea. At the same time promote every thing about Eritrea.
    NO BODY WANTS TO KNOW ABOUT ERITREA. IT IS UPTO THEM! PERIOD.
    2. I want you the reader will prove it.
    3. I know you will delete this comment again.
    Let me give this website another nice name : zeshabiya.com

  4. በእዚህ ዶማ በሆነ ብዕርህ የምትተፋው ትፋትህ ሰው አሳምናለሁ ብለህ መነሳትህ እራሱ የደደብነትህ አንዱ መገለጫ ነው::አንተ የባንዳ ልጅ ነህ::እንደት የነአ አጤ ምኒልክ ስራ ሊገለፅህ ይችላል::አንተ በወያኔ ሽንት የተጠጠመክ ሆነህ ሳለህ እንደት የሀይለ ስላሴ ለሀገር ተቆርቃሪነት ሊገባህ ይችላል?አተ የማታፍር ደነዝ ኤርትራ እትዮዽያ ከሆነች ጣሊያን ቅኝ ግዛት ገዝታናለች ማለት ነው ብለህ ትመፃደቃለህ::አንድ ሀገር ቅኝ ግዛት ተገዝታለች የሚባለው ሙሉ ግዛታዋ ሲያዝ ብቻ ነው::ኤርትራ የኢትዮዽያ አካል ባትሆንማ እነ ተመስገን ገብሬ ገንዘባቸውን ናጊዜያቸው ባላቃጠሉ::ለምን ለሱዳን ለኬንያ አረዱም::ስቃይዋ ስቃያቸው ስለሆነ ብቻ እንጂ::አፄ ቴዎድሮስ የሽዋ ሰውችን እግር ሲቆርጡ ከነበረ ት/ቤት በስሙ ባልተሰየ መለት ነበር::እንደ አሁኑ በምንግስት ተፅኖ እንዳ ይመስልህ::አንተ የቅድመ አያቶችህ የባንዳነት ታሪክ እያሳፈረህ ነው እንድህ የምትዘላብደው?ወያኔወችም ከዚህ የዘለለ ምክንያት የላቸውም::ኤርትራ ለመገንጠላዋ ከወያኔና ከሻቢያ ውጭ ማን ተጠያቂ ልታደርግ ነው::ስለህዝቡማ ኦሮማይን አንብብ::አንተኮ ከባንዳውች ቅደመ አያቶችህ የሚለይህ ቢኖር በዚህ ዘመን ላይ መሆንህ ብቻ ነው::

  5. asamagn tarikawi chibtochin akrben kememuaget ylq, tsehafiwn ena websitun mezlef yedkmetachin wanegnaw mlkt new. eske meche yhon mlashachin sdbna..zelefa hono yemiqetlew…? yh yaltegera yesdnet tsebay ewn yegna ye ethiopiawyan newn…? mengesha yetebalew tsehafi laqerebew tntanie lemn berega menfes mlashun lemestet anchilm…? lemnd new lesdbna lezelefa yemnchakolew…? sewn “wsha” blo yemisadeb…esu rasu wsha mehonu ayawqmn…? ..ebakachihu…enregaga.., huliem kegna amelekaket gar bcha yemihied tshuf endiqerbln antebq. yh ye yehasab netsanetn megedebna manquashesh new…!! ke Aabatochachin yeweresnew esiet sewn mezlefna manquashesh aydelem….!!

  6. ፩ የትግራይ ስርወመንግስት ያልከውን ግልፅ ብታረግልን፣ ምክንያቱም በኢትዮጲያ ታሪክ እንዲህ የሚባል ስርወመንግስት እንደነበር ዛሬ ገና ካንተ ሰማሁ። ኸየት አመጣኸው ይሆን?
    ፪ ለኤርትራ መገንጠል ተጠያቂ ማነው የሚለውን ነገር እርሳው፣ እኛ ኢትዮጲያውያን እኮ ኤርትራውያንን ከረሳናችው ዘመን የለንም። ራሳቸውን መመገብ ካቃታቸው ትናንት ጦር ያስታጥቁዋቸው የነበሩትን ዐረቦችና ኢምፔሪያሊስቶች ይጠይቁ።
    ፫ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ሲያገለግሉ የኖሩትን ባለሙያ ብስለት-ዐልባ ለማለት መድፈርኽ ለትዝብት የሚዳርግህ አንጂ የሳቸውን ክብር ቅንጣት ታኽል እንኳን አይቀንሰውም። ለመሆኑ አንድን በሙያቸው አንቱ የተባሉ ዓለምአቀፍ የህግ ባለሙያ ለመተቸት የሚያስችል ብቃቱ አለህ? ካለህ እሰቲ የትምህርት ደረጃህንና የሥራ ልምድህን ግለፅልንና እንቀበልህ፤ እግረመንገድህንም በቀድሞ መንግስት ተዘርግቶ የነበረው የራስ ገዝ ሽንሸና ለምን በህግ ተቀባይነት እንደማይኖረው ዓለምአቀፍ ህጎችን፣ ውሎችንና የፍርድ ውሳኔዎችን እያጣቀስክ ብታስረዳን?
    ፬ የሀገራችንን ታሪክ በተመለከተ ልዩነቶች ሊኖሩን ይችላሉ፤ ለ’ኔ ያ አሳሳቢ አይመስለኝም። አሳሳቢው የወደፊት ዕጣችንን በተመለከተ ያለን ልዩነት ነው። ሁሉም በእኩልነት ላይ የተመሰረተች የግለሰብና የቡድን መብት መከበር የተረጋገጠባት ኢትዮጲያን እንደመፈለግ፣ ሀገርን እንደዳቦ እየቆረሱ ለባዕድ የሚቸበችቡና፣ ህዝቡን እያስራቆቱና እያስራቡ ቢሊዮን ዶላር ወደውጭ የሚያሸሹ ባንዳዎች ሀገሪቱን እያጠፉዋት ነው።

  7. Mengesha,

    One thing we know for sure is that every historical fact has two sides and explanations. In most cases what remains as a fact is the one written by a victor or the dominant political force. We regurgitate those facts and brain wash the society with it that it becomes fixated. Once fixated, it only takes weak minds to fly with those “facts” like the ones parroting here as commentators. The tragedy of Ethiopia is that we lack a common history as we are an amalgam of nations forced to live together. I know there are historians and politicians who would like make us one people when they know for sure that we are not. It was in the high school that we were fighting against each other in Addis Ababa because of our ethnicities.TPLF did not create Amhara, Oromo, Tigre. It was there in every day life. People wanted to ignore it. Today we are going apart with a speed hard to catch. You cannot mix immiscible stuff.

  8. ፭ ኢትዮጲያውያን በቀይባህርና በወደብ ጉዳይ ላይ የሚያነሱት የይገባኛል ጥያቄ ቋቅ የሚልህ ምን ዐይነት ጉደኛ “ኢትዮጲያዊ” ብትሆን ነው ባክህ?
    ፮ ሀገራችን በቅኝ ባለመገዛትዋ የሚሰማንን ኩራት መመፃደቅ ብለህ ማጣጣልህ ምን ያህል “ኢትዮጲያዊ” ስሜት እንዳለህ የሚያሳይ ነው። የሚገርምህ ግን የኢትዮጲያን አኩሪ የነፃነት ታሪክ ጠላቶቻችን እንኳን የሚመሰክሩት ነው። ሀገራችንን በቅኝ ለመግዛት ካንድም ሁለት ጊዜ ያልተሳካ ሙከራ ካደረገችው ኢጣሊያ እንኳን የረዘመ የነፃነት ታሪክ ባለቤት ነህ። አንተን ቋቅ ቢልህም ወይም መመፃደቅ ቢመስልህም ለኛ ግን ብሄራዊ ኩራታችን ነው።

  9. ba hiywote yatiliki saw dadab lamajamariya gize siya gatimagn yamtsaf chilotahin lamadnaqi gin tatitehi now wayis sati tata matsFIHIN BICHa mawaki faligalaw tarkin tsfahi wagan kamatrafih tarkin azabtehi wagan mabalashatihin hilinahi yiwqasihi laqitash sitiyi indamiti chiri gabtonal taradtenilishal jalase baharfa wuraji tabano bishal

  10. ፀሃፊው በኤርትራ ጉዳይ ላይ በሚያቀርባቸው ጭብጦች ዙርያ ብዙ የማውቀው ነገር ስለሌለ እውነት ነው ወይም ውሸት ነው ለማለት ባልደፍርም…የእርሱን ሃሳብ በተጨባጭ ማስረጃዎች በመሞገት ፋንታ በፀሃፊው ላይ የስድብ ናዳ ማዝነብ ግን የተሸናፊነት ምልክት ይመስኛል ። ከኛ የተሰወሩ ወይም ደግሞ ሆን ተብለው የተንጋደዱና የተዛነፉ ብዙ ታሪኮች መኖራቸው እርግጥ ነው!! ለምሳሌ ያህል የአፄ ምኒልክን ጨፍጫፊነት በተመለከተ መንገሻ ያነሳው ነጥብ እውነት ከመሆኑም በላይ በሁሉም የኦሮሞ ልጆች ልብ ውስጥ ያለ ነገር ነው ። ይህ አይነቱ ታሪክ ግን ሆን ተብሎ እንዲድበሰበስ ተደርጓል ። የምኒልክን ጨፍጫፊነት ማንሳት የአማራ ተወላጆችን እንደማጥቃት ተደርጎ የሚወሰድበት ጊዜ እጅግ ብዙ ነው ። ይህ ደግሞ ገዥዎቻችን ሆን ብለው ያሰረፁብን በሽታ ነው ። ስለሆነም..የምኒልክ የጨፍጫፊነት ታሪክ ሲነሳ ከማንምና ከምንም በላይ በቅድሚያ የሚንጫጩት የአማራ ተወላጆች ናቸው። ይህ ለምን ይሆናል..? ፀሃፊው አቶ መንገሻ ሊበን እንዳለው…. የምኒልክን አረመኔነት ለማወቅ የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ ካለ..አሁንም ወደ ኦሮምያ በተለይም ደግሞ ወደ አርሲ መጥቶ ታሪክ እንዲመረምር ነው የምንጋብዘው ። አዲሱ ትውልድ የሚማረው ከዚህ ሆን ተብሎ ወደ አንድ ወገን ብቻ ካጋደለ ታሪክ መሆን የለበትም ። የምኒልክ ታሪክ የአማራ ታሪክ ነው ብሎ የሚሞግት ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለኝም። እውነታው ያ ከሆነ…የምኒልክ ስም ሲነሳ አልያም ምኒልክ ሲወቀስ አንድን ብሄር ብቻ በተለየ ሁኔታ የሚያንጫጫበት ምክንያት ያለ አይመስለኝም። ምኒልክ አልያም ሃይለስላሴ ለምን ተነኩብን ብሎ የሚቆጭ ካለ ግን፣ ምናልባት የተንጋደደው ታሪክ ተጠቃሚ አልያም ደግሞ የእነርሱ ርዝራዥ መሆን አለበት ። ስለሆነም የስድብ ጋጋትን ከማዝነብ ይልቅ በበስለትና በረጋ መንፈስ ለመማር የሚበጁንን ጭብጦጭ ብናቀርብ ለሁላችንም ይበጃል እላለሁ ።

  11. የኢትዮጵያና የኤርትራን ታሪክ በተመለከተ መንገሻ ባነሳቸው ነጥቦች ዙርያ ባብዛኛው ባልስማም ሆን ተብለው የሚደበቁ ታሪኮች መኖራቸው ግን የማይካድ ነገር ነው ። በእርግጥ እነዚህ ታሪኮች የሚደበቁት ለአገር ደህንነት ወይም ለገዥዎች ህልውና በሚል ምክንያት እንደሆነ አያጠራጥርም። ስለዚህ ዋናው ነጥብ መሆን ያለበት ከዚህ የተደበቀ ታሪክ ምን መማር አለብን የሚለው ነገር ነው ። በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የፖለቲካ አጀንዳ ውስጥ የኤርትራ ጉዳይ የተረሳና ያለቀለት ጉዳይ ነው ብሎ መደምደም የሚቻል አይመስለኝም ። ወደድንም ጠላንም ሁለቱ ህዝቦች እሰከመቸውም ቢሆን ተራርቀው ሊኖሩ አይችሉም ። አንድ አስተያየት ፀሃፊ እንዳሉት “ ወይ እነርሱ ያጠፉናል..ወይም እኛ እናጠፋቸውለን ” እያሉ መፎከር ግን ጤነኛ አእምሮ ካለው ሰው የሚጠበቅ ንግግር አይመስለኝም ። እንዲያውም የለየለት እብደት ነው !!። ሙሴ የተባለው ግለሰብ በሰጠው በሳል አስተያየት ላይ በአብዛኛው እስማማለሁ !! ዶክተር ያእቆብን በተመለከት በሰጠው አስተያየት ላይ ግን እኔም የራሴ ተቃውሞ አለኝ ። ለመሆኑ የዶ/ር ያእቆብ የህግ አዋቂነት ለኛ ኢትዮጵያዊያን የፈየደልን ምን ነገር አለ..? እኛ ኢትዮጵያዊያን ከዶ/ር ያእቆብ ህግ አዋቂነት የተጠቀምነው ነገር ምንድን ነው…? በአገራችን እየተፈፀመ ያለውን የዘር ጭፍጨፋ ለማጋለጥ አልያም ጨፍጫፊዎችን ለህግ ለማቅረብ በህግ ምሁርነታቸው ያደረጉት ጥረት አለን..? የርዋንዳን የዘር ፍጅት በማጣራት ረገድ ብዙ እንደሰሩ የሚነገርላቸው ዶ/ሩ …በአገራችን በተፈፀሙት ጭፍጨፋዎች ዙርያ ምን የተናገሩት ነገር አለ ? ትላንትና ከትላንት ወዲያ ምንም አይነት ወንጀል የሌለባቸው ንፁሃን ዜጎቻችን በበደኖና አርባጉጉ በጅምላ ሲጨፈጨፉ ዶክተር ያእቆብ የት ነበሩ..? ትላንትና ከትላንት ወዲያ በጋምቤላ ህዝብ ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው አሰቃቂ ወንጀል ሲፈጸም ..ያእቆብ ምን ተነፈሱ ..? ትላንትና ከትላንት ወዲያ ደርግ እንቦቃቅላ ወጣቶችን የፍየል ወጠጤ እያዘፈነ በየመንገዱ ሲረሽናቸው፣ ወያኔ ደግሞ በፊናው የህዝብ ድምፅ ይከበር ስላሉ ብቻ በጠራራ ፀሃይ በየአደባባዩ ሲጨፈጭፋቸው ዶክተሩ አለማቀፋዊ የህግ ምሁርነታቸውን ተጠቅመው ምን አደረጉልን…? ከአማራነታቸው በቀር አንድም ወንጀል የሌለባቸው ሰላማዊያን ወገኖቻችን ከየክልል እየተለቀሙ ሌጣቸውን ሲባረሩ በአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ላይ ቀርቦ ከመደስኮር ውጭ ዶክተሩ የክስ ፋይላቸው ለዓለማቀፉ የወንጀለኞች ችሎት አቅርበዋልን…..? እውን የዶክተር ያእቅብ ትግል ለህዝብ ጥቅም ነው ወይስ ለስልጣን…? ዶክተር ያእቆብን በተመለከት በተፃፈው የሙሴ አስተያየት ዙርያ ብዙ ነቀፌታዎችን ማቅረብ በተቻለ ። እርግጥ ነው ዶክተር ያእቆብ ታዋቂ ናቸው ። ታዋቂነታቸው ብቻውን ግን ሁሉን ነገር ‘አዋቂ’ ሊያደርጋቸው አይችልም ። ከዚህ ውጭ ግን ዶክተሩንም ሆነ ሌሎች ሊህቃንን ለመንቀፍ የግድ እንደነርሱ አለማቀፋዊ እውቅናን ማትረፍ አልያም ደግሞ ማስተርስና ፒ.ኤች.ዲን መያዝ አይጠይቅም ።ስለዚህ በዚህ ዙርያ ከሙሴ ሃሳብ ጋር አልስማማም ። ለማኝናውም በመንገሻ ፅሁፍ ዙርያ የሚሰጡት አስተያየቶች ከግላዊነት ይልቅ አገራዊ አጀንዳ ላይ ቢያነጣጥሩ የተሻለ ነው የሚል አመለካከት ነው ያለኝ ።

  12. This article is the worst ever I read from this website. It has no any substance to give for reader. Some weeks ago I read also another article which was written from this so called writer. Seems the articles were written by fresh cadre who has no any idea how to write articles. No coherence, no flow, no reference…..etc . It is simply good for nothing. What surprised me a lot is, he got shortage of time to write this vulgar article!!!! He would like to add more crap if he got time!!!!! ‘’Wey gud’’
    Mr. Mengesha Libenn: reading should come first before writing. Come again another time after you read well.

Comments are closed.

Share