May 31, 2013
3 mins read

“ዐማራው በአገር አትኖርም ተብሎ እየተባረረ ኤርትራውያን ባለመብቶች ሆነው በአገሪቱ ንብረት ይዝናናሉ” ሞረሽ

(ዘ-ሐበሻ) ሞረሽ ወገኔ የሚባለው የአማራ ድርጅት “የኢትዮጵያ አንድነት መልካም ውርስና ቅርሶቹን ተጠብቆና በእነርሱም መሠረትነት ዳብሮ መቀጠል አለበት ብላችሁ ለምታምኑ ኢትዮጵያዊትና ኢትዮጵያውያን!” በሚል ርዕስ በበተነው መልዕክት ” በምርጫው ሳይሆን ፣በተፈጥሮ ሕግ ምክንያት የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አማርኛ ከሆነ ወላጆች የተወለዱ የነገደ ዐማራ ማኅበረሰብ አባላት ባለፉት የትግሬ ወያኔ ዘረኛና ናዚያዊ አገዛዝ፡-
 በኢትዮጵያዊነት ብሔርተኝነት አራማጅነት፣
 በኢትዮጵያ አንድነት ጠበቃነት፣
 በነፍጠኝነት፣
 በትምክህተኝነት፣
 በአድኃሪነት፣
 በጨቋኝ ብሔርተኝነት፣
 በገዥ መደብነት ፣ ወዘተርፈ
ፈርጆ የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ወንጀል የተፈጸመበትና እየተፈጸመበት ያለ መሆኑ በደቡብ፣ በኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በሶማሊያ፣ በቤንሻጉል ጉምዝ ይኖሩ የነበሩ ዐማሮች በዘራቸው ምክንያት በወረንጦ እየተለቀሙና በቀን መብራት እየተፈለጉ በወታደራዊ ኃይል በታገዘ አፈና እየታፈሱ መባረራቸውንና በርካታዎቹም መገደላቸው ይታወቃል፡፡ ይህ ድርጊት በየትኛውም ዘረኛ፣ ፋሽስትና አምባገነን አገዛዞች ያልተደረገ፣ በኢትዮጵያ በዘረኛው የወያኔ ትግሬ አገዛዝ ለመጀመሪያ ጊዜ አካባቢዎችን ከአንድ ዘር የጸዳ የማድረግና ይህንኑ ዘር አድኖ የማጥፋት ተግባር በማን አለብኝነት ሲከናወን እያየን ነው፡፡” አለ።
“ኤርትራውያን ኢትዮጵያዊ አይደለንም፣ በኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት የተያዝን ነን ብለው ለ30 ዓመታት ታግለው፣ በወያኔ የመገንጠል መብት አገኝተው፣ ከተገነጠሉ በኋላ በአገሪቱ ሁለንተናዊ ሀብት ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ እየተደረገ ነው፡፡ ዐማራው በአገር አትኖርም ተብሎ እየተባረረ ኤርትራውያን ባለመብቶች ሆነው በአገሪቱ ንብረት ይዝናናሉ፡፡” ያለውን የሞረሽ መል ዕክት ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

2 Comments

  1. guys take care when you talk about muslims and Galas/Oroms. You have to know there was some truth in what Italy was doing fro others. You have to have a mind seting of NO ONE IS FREE UNLESS WE ALL ARE FREE and HUMANITY BEFORE ETHNICITY. We have no right to object the spread of Islam or the use of ones own languge as far as it is done in a peaceful and acceptable way without compromising the basic human right of others. otherwise I am in to fight weyane but to for superority but equality.

Comments are closed.

defence minster
Previous Story

ምንድነው ጉዱ?

eprpyl 1
Next Story

የኢሕአፓ ወጣት ክንፍ ከሰማያዊ ፓርቲ ጎን እንቁም አለ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop