በሚኒሶታው ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ ዙሪያ እኔም የምለው አለኝ – ከፕ/ር ቤካ መገርሳ

ከፕሮፈሰር ቤካ መገርሳ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፥ አሜን።

“ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በእርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በእርሳችን እንመካከር እንጂ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።” ዕብ ፲፥ ፳፬-፳፭
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍሥሐ ወሰላም
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓል (በደብረ ምጥማቅ የታየችበት ዕለት) በሰላምና በጤና አደረሰን፥ አሜን። ከላይ እንደ መግቢያ የተጠቀምኩት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለዕብራውያን ወገኖቹ የጻፈውን መልእክት ነው። ቀለል ባለ አማርኛ ሲተረጎም ‘ቀኑ ሲቀርብ ስታዩ፣ የፍቅርን መቀዝቀዝ ስትመለከቱ፣ የወንድማማችነትና እኅትማማችነትን ጣዕም መቀነስ ስትገነዘቡ ተሰብስባችሁ ተመካከሩ ይህ ለፍቅርና መልካም ሥራ ስለሚያነቃቃችሁ’ እንደማለት ነው። ለመጻፍ ያነሣሣኝ ምክንያት ቢኖር ሰሞኑን ወንድሞችና እኅቶች ስለ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የወደፊት ዕጣ የተጻጻፉትን የተለያዩ ሃሳቦች ከተመለከትኩኝ በኋላ ነው።
የፊታችን እሁድ ጁን 2 ቀን በደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምርጫ ይደረጋል ተብሏል።ታላላቅ ወንድሞችና እኅቶች፣ አባቶችና እናቶች በተለይም ካህናተ ቤተ ክርስቲያን ላለነውም ሆነ ለመጪው ትውልድ ኃላፊነት አለብን። ይህ ኃላፊነታችን ከሁሉም በላይ በተለያዩ ምክንያቶች የመጣነውን በሙሉ በመንፈሳዊ ህይወት አሳድጎ በመልካም ሥነ ምግባር የታነጸ ትውልድን ማፍራት ነው። መንፈሳዊ ህይወት ማለት ደግሞ መመሪያውን መጽሐፍ ቅዱስ በማድረግ ዓለምን ከሁሉ በላይ በሆነው መንፈሳዊ ጥበብ መቃኘትን ያመለክታል። መንፈሳዊ ህይወት እውነት ነው፤ መንፈሳዊ ህይወት ጀግንነት ነው፤ መንፈሳዊ ህይወት መተሳሰብ ነው፤ መንፈሳዊ ህይወት ትዕግሥት ነው፤ መንፈሳዊ ህይወት አርምሞ (ፀጥታ)ነው፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ መንፈሳዊ ህይወት በማስተዋል መጓዝ ነው ይህን ካደረግን ነው ለእኛ ሲል የተሰቀለውን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ልንመስለው የምንችለው ይኸውም ፍቅርን እንለብሳለን ማለት ነው።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሰው የሆነው ስለ ሁለት ዐበይት ነገሮች ነው፤ አንደኛው እኛን ከራሱ ጋር አስታርቆ በኃጢአታችን ምክንያት የተነጠቅነውን ጸጋ ለመመለስ እና ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ እርሱን አምነን ለምንጓዝ ምዕመናን በሙሉ ክርስቲያናዊ ህይወት ምን መምሰል እንዳለበት ለማስተማር ነው።
ቤተ ክርስቲያን መመላለስ ክርስቲያናዊ ህይወታችንን ያጠብቀዋል፣ ያለመልመዋል። አእምሮአችን ይሰፋል፣ ጥበብ ሥጋዊና ጥበብ መንፈሳዊ ይሰጠናል። በመንፈሳችንም ሆነ በሥጋችን እንጠቀማለን፤ በመንፈሳችን የምንጠቀመው ሳምንቱን ሙሉ በተለያዩ የዓለም ነገሮች ተይዘን ለጸሎት ጊዜ አጥተን የነበርነው ወይም ከሰዎች ጋር በተለያዩ ምክንያቶች ተጋጭተን የነበርነውን የጸጥታ ወደብ የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ስንመጣና ንስሐ ስንገባ፣ ስንጸልይ፣ ስንሰግድ፣ ስናስቀድስ፣ የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ስንቀበል ደስ ይለናል ይልቁንም ሐሴትን እናደርጋለን፤ ለበለጠ ሥራ እንነቃቃለን። በሥጋዊ ሕይወታችንም ቢሆን ቤተ ክርስቲያናችን በጣም ትጠቅመናለች። ሌሎች ብዙ እየሰሩ ‘ገንዘብ አይበቃንም’ እያሉ ሲጨነቁ ክርስቲያኖች ግን ‘የምንኖርበት ኑሮ ይበቃናል’ በማለት ከሚያገኙት ደሞዝ አሥራት(አንድ አሥረኛውን)ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በመሥጠታቸው የተረፋቸውን ገንዘብ እግዚአብሔር አምላክ ሲባርክላቸው እንመለከታለን፣ ጤንነታቸውን ጉልበታቸውን አእምሮአቸውን ሲባርክላቸውና ለማዕረግ ሲያበቃቸው እናያለን አይተናልም።
ይህ ኹኔታ ቤተ ክርስቲያናችንን እስከ መጨረሻው ጊዜ ድረስ እንድንጠብቃት ያደርገናል፣ መንፈሳዊ መጨከንን ያስጨክነናል። ከሁሉ በላይ ቀደም ሲል እንዳልኩት ማስተዋልን የምናገኝባት ቦታ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው መልእክቱ “መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል ራሱ ግን በማንም አይመረመርም።” (፩ ኛ ቆሮ ፪፥፲) ብሎ እንዳስተማረን ከጥበብ ቦታ ጥበብን በደንብ አድርገን መግዛት አለብን፣ ሲያልቅብንም መሙላት አለብን። ክርስቲያኖችን እስከመጨረሻው ድረስ የሚጠብቃቸው የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅዱሳን አማላጅነት ጥባቆት ነው። እግዚአብሔር ለእኛ ለኃጢአተኞቹ ቸር ነው፤ ይህንንም የምናውቀው እና የምናዳብረው መንፈሳዊ ጥበብን ሊሰጡን የሚችሉ መጻሕፍትን ስናነብ ነው። “የዕለት እንጀራችንን ስጠን ዛሬ” ብለን ስንጸልይ ገንዘብ ብቻ እንድናገኝና እንጀራ እንድንገዛበት ማለቱ አይደለም ምክንያቱም ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርምና ነገር ግን በፈጣሪም ቃል እንጂ። አንድ ሰው ደግሞ ከእግዚአብሔር ቃል ካልተለየ ቢወድቅ አይሰበርም፤ አምላኩ አይለየውምና። እራሱን ደካማ ያደረገ ሰው ኃያሉ መንፈስ ቅዱስ ይቀርበዋል፤ ራሱን አለሁ አለሁ የሚል ግን ደካማው ሰይጣን መሣሪያው ያደርገዋል።
ይህን ለማለት የተገደድኩበት ዋና ጉዳይ ሰሞኑን እየተጻፉ ካሉት አንዳንድ ጽሑፎች በመነሣት ነው። እንደ እኔ እምነት ኢሳት፣ ቪኦኤ፣ ኢትዮ ሚድያ፣ ዘሐበሻ ሌሎችም በሙሉ መረጃ ያቀብላሉ መረጃውን ተቀብሎ እርምጃ መውሰድ የባለቤቱ ድርሻ ነው። እንደ ክርስቲያን ግን እነዚህ በሙሉ መመሪያዎች ሊሆኑ አይገቡም እላለሁ። መመሪያችን መሆን ያለበት መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ክርስትናችን የተግባር ክርስትና (applied Christianity) መሆን አለበት። ይህም ማለት የቤተ ክርስቲያን ነገርን በተመለከተ ስንጽፍ መረጃችን መመሪያችን በቅድሚያ መጽሐፍ ቅዱስ መሆን አለበት ማለት ነው። ማንም አስተዋይ ሰው እናት አገሩን የማይወድ የለም፤ በእኔ አመለካከት ደግሞ እናት አገር ማለት አፈር ሸንተረር ወንዝ አየር ብቻ ሳይሆን ከሁሉ በላይ በአገሩ ላይ የሚኖር ማንኛውንም ወገን የሚያጠቃልል ነው። ወገን ሲሰደድ አብሮ መሰደድ፣ ሲያዝን አብሮ ማዘን፣ ሲደሰት አብሮ መደሰት ሰብአዊ ባሕርይ ነው። ከሁሉ በላይ ደግሞ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይህን ነገር በየዕለቱ ታከናውነዋለች (ይህም ይታወቅ ዘንድ በእንተ ቅድሳት የሚባለው ክፍል ላይ ዲያቆኑ የሚያነበውንና እኛም “አሜን አቤቱ ይቅር በለን” እያልን የምንመልሰውን ማስተዋል ይገባል)።
እርግጥ ነው ይህ በቂ ስላልሆነ ካህናተ ቤተ ክርስቲያን ስለ አገር ስለ ወገን መስበክ ይጠበቅባቸዋል፣ በተለያየ ይዘትም ሲያደርጉት እናያለን። ስለዚህ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በላይ ስለ አገር የሚሰብክና ጠንቅቆ የሚያውቅ የለም ብዬ አምናለሁ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስል ደብረ ሰላምን ብቻ ማለቴ አይደለም በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ማለቴ እንጂ። በዘመናችን የሚድያ ቴክኖሎጂ መስፋፋትን ተከትሎ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ኹኔታ በየቀኑ እንሰማለን፣ እንወያያለን። በአገር ቤት ያሉ ምዕመናን የእኛን ያህል መረጃ የላቸውም ብል ማጋነን አይመስለኝም ምክንያቱም እኔም ራሴ በግሌ አገር ቤት በሄድኩባቸው ወቅቶች ከመረጃ መራቄን ስለማውቅ ማለት ነው።
‘እግዚአብሔር የለም’ ብሎ የሚል አንድ ኢአማኒ (atheist) የእግዚአብሔርን መኖር እንደማያስቀረው ሁሉ አገር ቤት ምንም ዜና አለመሰማቱ ችግር የለም ማለት አይደለም። በእኔ እምነት ቤተ ክርስቲያናችን ላለፉት ሃያ ዓመታት ያሳለፈችው በራሷ ልጆች የመበላትና የመጎዳት ዕጣ መቼም አልታየም። እዚህ ላይ ይህን ስል
ለመታረም ዝግጁ ሆኜ ነው። ቀደም ሲል እንደተናገርኩት መረጃ የማግኘት ዐቅማችን በማደጉ ብዙ የአሁኑ ጊዜ ጥፋቶች ታይተውን ይሆናልና ቀደም ሲል በነበሩ የቤተ ክህነት ሥራዎች ውስጥ ለነበሩና የበለጠ ለሚያስረዱ እተወዋለሁ። ቢሆንም ግን ሰሞኑን ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ከተወረወሩት ጽሑፎች እንዳየሁት የመንግሥት ባለሥልጣናት ቤተ ክርስቲያናችንን ለማጥፋት አርፈው የተቀመጡበት ጊዜ የለም ወደፊትም አይኖርም። ይህ በቅጡ የሚወገዝ ተግባር ነው።የቅዱስ አቡነ ጴጥሮስን ስም እያነሡ ቅዱስነታቸው የሠሩትን ሥራ አለመሥራት ግን ጀግና አያስብልም። የመንግሥት ተቃዋሚ መሆን አንድ ሥራ ነው ተቃዋሚ ብቻ ግን መሆን አያስፈልግም ተቃውሞ ጀርባ መሠራት ያለባቸውን ነገሮች መሥራት እንጂ። እንደኔ እምነት በልመና ላይ ያለን ሰው ሁልጊዜ ገንዘብ ከመስጠት ባሻገር ራሱን የሚያሻሻልበትን ኹኔታ መፍጠር ጀግንነት ነው። እንደዛው ሁሉ በአሁኑ ሰዓት ያሉትን የመንግሥት ፖሊሲዎች መቃወም አንድ ነገር ሆኖ ሳለ ባለንበት አገር ውስጥ ተደራጅቶ ድምጽ እንዲሰማ ማድረግ ሌላ ነው። ይህን አመለካከትና አካሄድ ግን ወደ ቤተ ክርስቲያን ለማስገባት ከሞከርን ሌላ መልክና ቅርጽ ይዞ ችግር ይፈጥራል። አገራችን ኢትዮጵያ መልካም አስተዳደር እንዲኖራትና በመንግስትም ሆነ በቤተ ክህነቱ በኩል ቅንና አስተዋይ መሪዎች ታገኝ ዘንድ በየትኛውም ዓለም ያለች ቤተ ክርስቲያን ከመጸለይ ወደ ኋላ አትልም።
፮ኛው ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከመሾማቸው በፊት በቅን ወገኖች አማካይነት ዕርቀ ሰላም ተጀምሮ እንደነበር ለሁላችንም ግልጽ ነው። ሁላችንም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች በከፍተኛ ጉጉት ላይ በነበርንበት ወቅት ከአንድነት ይልቅ መለያየትን፣ ከፍቅር ይልቅ ጸብን የሚሰብከው ሰይጣን በግብር ልጆቹ አማካይነት አፈረሰብን። ለጊዜው በኹኔታው ያልተናደደ ያልተቆጨ ሰይጣንና ሠራዊቶቹ ብቻ ናቸው ብል ማጋነን አይሆንም። ነገር ግን ….ይህ ኹኔታ ታላቂቱን ደብር ደብረ ሰላምን በመዋቅር ሥር ከመክተት ወደ ኋላ የሚያደርግ አይሆንም። ይህን የምልበት ዋናው ምክንያት ‘የቄሣርን ለቄሣር፣ የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር’ ከሚል አስተሳሰብ ተነሥቼ ነው። ልክ ነው አንዳንድ ባለጌ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት በማያገባቸው ገብተው ቤተ ክርስቲያናችንን ሲሰድቡና ሲሳለቁባት እናያለን፤ እንደውም መናፍቅነታቸውን ባጎላ መልኩ አዳዲስና ባዕድ ባህል እያስገቡ ቤተ ክርሰቲያኒቷ ባለቤት እንደሌላት ሲያድርጉ ይስተዋላሉ። እዚህ ያለንበት አገር መጥተው እንደልባቸው መፈንጨት ስለማይችሉ ያችው ምስኪኗ አገር ቤት ያለችውንና በየዕለቱ የምትሳቀቀው ቤተ ክርስቲያንን ሲላገጡባት እንሰማለን፤ ለእነርሱም የሞተላቸው አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልቡና ይስጣቸው እላለሁ እንጂ እነሱ በሚናገሩበት ዝቅ ያለ ቋንቋ እኔ አልናገርም ባህሌም መንፈሳዊ ኑሮዬም አይፈቅድልኝምና። ይህን እየተናገሩ ቤተ ክርስቲያኔን ለመከፋፈል ለሚጥሩ ሐራ ሠገራት ግን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እጄን አልሰጥም። ለዚህ ነው በአቋም ደረጃ የቤተ ክርስቲያን መዋቅር ሥር እንሁን የሚል አስተሳሰብ ያለኝ። የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ወደ መዋቅር ሥር ትግባ ማለት ከወያኔ ጋር ትቀላቀል ማለት አይደለም፤ ከአድርባይ የቤተ ክህነት መሪዎችም ጋር እንተባበር ማለት አይደለም።
የዛሬን ሳይሆን የነገን ሳስብ ግን ምናልባት እግዚአብሔር ቢፈቅድ አንድ እየሆንን ስንሄድ መንፈሳዊ መሪዎቻችን የሆኑት ጳጳሳትም ልቡና ገዝተው ፍርሃትን አርቀው ደፋሮች ጀግኖች ሆነው ቤተ ክርስቲያናችንን ወደ ቀደመ ቅድስናዋ ይወስዷታል ብዬ በማመን ነው። የመጪው ግንቦት ፳፭ (June 2) ስብሰባም መሆን ያለበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስብሰባ እንጂ ልክ ከዚህ በፊት አብረው ሻይ ቡና እንዳልጠጡ ወንድማማች እኅትማማች ሆነን አንደኛው ወገን የቤተ ክርስቲያን ተቆርቋሪ፣ ሌላኛው ወገን ቤተ ክርስቲያንን አሳልፎ ሰጪ ሆኖ መታየት የለበትም። ማንም አሸናፊና ተሸናፊ የለም፤ ሁልጊዜም ቢሆን አሸናፊነታችን ለመድኃኔዓለም ነው። ካለንበት አገር አሜሪካ የምንማረው ነገር ቢኖር ሰዎች የተለያዩ አስተሳሰቦችን ይዘው ቀርበው ሲከራከሩ ውለው የማታ ማታ በሰላም ተለያይተውና ተግባብተው ስናይ እኛ ቤተ ክርስቲያን የምንመላለስ ምዕመናን ከእነርሱ በልጠን መገኘት እንዳለብን ይሰማኛል። ካህናት አባቶቻችንን እናክብር፤ ምንም ይሁን ምን በመንፈስ ቅዱስ ተቀብተው እኛን ሊያስተምሩን ንስሐችንን ሊቀበሉን ለነፍሳችን የሚሆን ሥንቅን ሊሰንቁን ከእግዚአብሔር ተሹመዋልና። እርስ በእርሳችን እንከባበር ብናስተውለውም ባናስተውለውም መድኃኔዓለም ስለሁላችን ነው የተሰቀለው እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያምም ስለሁላችንም ነው የተሰደደችው። የሰበካ ጉባዔ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በሚያወጡልን መመሪያ መሠረት የስብሰባውን መርሐ ግብር እንከታተል እንታዘዛቸውም።በእምነት የጸኑትን እናስባቸው። መከራ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሲደርስባቸው ቤተ ክርስቲያናቸውን ሊያቃጥሉባቸው ሲሹ ታቦተ ህጉን ይዘው ወደ ጫካ የገቡትን፣ ‘ከነታቦቱ ቅበሩን እግዚአብሔር የፈቀደው ትውልድ ይጠቀምበት’ ያሉትን አናስባቸው እንጂ ለንደን እንዲህ ሆነ ዳላስ እንዲህ ሆነ ብለን አንፍራ።
እነርሱ ጋር የደረሰው እኛ ጋር ሊደርስ የሚችለው በጥላቻ መንፈስ ብቻ ተመልተን የምንነጋገር ከሆነ ነው። እኛ ከእነርሱ እንበልጣለን እንሻላለን የሚል መንፈስ ይዤ አልናገርም፤ ሁላችንም ሰዎች ነን እንበድላለን ነገር ግን በማስተዋል ነገሮችን ካደረግን ምናልባት ቅድም የጠቀስኳቸው በመጥፎ ምሳሌ እንደሚነሡ እኛ የመልካም
ነገር ምሳሌ እንሆናለን። እንዴ፥ ምነው በሰላም የተቀላቀሉ አብያተ ክርስቲያናት የሉም ወይ? ምሳሌ ካስፈለገ ምነው የቅርባችን የሳውዝ ዳኮታ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ስሙ የማይነሣው? በመመካከርና በጥበብ በማድረጋቸው ያለ ምንም ችግር ድምጻቸው ሳይሰማ አይደለም እንዴ በመዋቅር ሥር የገቡት?
ዋናው ነገር፥ ልበ ሰፊ ነገር አላፊ ሆኖ ለመወያየት መቅረብ ነው። ሁሉም ሰው በአንድ ጊዜ አንድ አይነት አስተሳሰብ ያስብ ማለት የዋኅነት ነው፤ ስለሆነም ወደ እናት ቤተ ክርስቲያን እንቀላቀል የሚል ወገንም ሆነ በገለልተኝነት እንፅና የሚል ወገን መንፈሳዊነትን ባልለቀቀና ፕሮፌሽናል በሆነ መንገድ የራስን ስሜት በመገደብ የቆሙበትን ቦታና ዓላማ ባለመዘንጋት በማስተዋል ሃሳብን ማስተላለፍ ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ። በሌላ ወገን ደግሞ በምዕመናን ላይ ጫና ለመፍጠር መሞከርና ስምን በመደበቅ የብዕር ስም እየተጠቀሙ ፍርሃትን ለመልቀቅ መሞከር መልካም ሥነ ምግባር አይደለም። ዝምታም ፈሪነት አይደለም።
የጀግና ስም ከጠሩ ጀግናውን ለመሆን መጣር ያስፈልጋል። ክርስቲያኖች መሠረታችን ፈጣሪያችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የክርስቶስ ከሆንን ደግሞ አይደለም በዘር ማጥፋትና በመለያየት ሃሳብ ላይ የተሰለፉ ወገኖች ብቻም ሳይሆኑ የገሃነም ደጆች ቤተ ክርስቲያናችንን ሊያናውጡአት አይችሉም፤ እኛ ብናንቀላፋ ፈጣሪያችን አያንቀላፋምና።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር
ቤካ መገርሳ
Professor
University of Saint Thomas
Mechanical Engineering Dep’t

ተጨማሪ ያንብቡ:  39ኛ የካቲት ለማክበር ሽርጉድ እና የተሟጠጠው የትግራይ ህዝብ ስሜት

13 Comments

  1. Endet leb west yemegeba meker!!!! Bet Egzehabeharen y- poleteka metekemya madereg ayegebam! Sewoch hager bet segebu yet hadew new yemesalemut? Lemanengawem Pr. Baca keleb saladenkot alalfem!

  2. በቅድሚያ ከስሙ ልነሳ,
    ምን አይነት ዘመን ነው ዘመነ መላጣ
    ለንቦጨሙ ሔዶ ለሐጫሙ መጣ ነው የተባለው

    ይሄ ፕሮፌሰርነት ዝም ብሎ የሚታደል ሆነ እንዴ፣ ድሮ ድሮ አሉ፣ ፒኤችዲ (PHD) ተይዞ ከፍተኛ የምርምር ውጤት ላመጡ ወይንም በመምህርነት የዶክተሪት ዲግሪያቸውን የያዙ እና በመምህርነት ሊቅ (ልህቃን) ለተባሉት ነበር ይህ ማዕረግ የሚሰጠው፤ ታዲያ ወንድማችን ቤካ መገርሳ (አውቃችሁ አብቅሉ – በአማርኛ ሲተረጐም) ገና ማስተሩን እንኳን ሳይጨብጥ እራሱን ፕሮፈሰር ብሎ መጥራቱ ለኔ – ጅብ እማያውቁት ሀገር ሔዶ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ እንደተባለው ነው። ከመፅሐፍ ቅዱስ ከጠቃቀስክ አይቀር – እራሳቸውን ከፍ ከፍ የሚያደርጉ ዝቅ ዝቅ ይላሉ ይላል አይደል ቅዱስ መፅሐፉ፣ ሰውን ማታለል ይቻላል የራስን ህሊና እና እግዚአብሐርን ግን በፍጹም ማታለልም ሆነ መሸወድም አይቻልም።
    ስለ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የበለጠ ለመረዳት ይህንን ሊንክ ይመልከቱ http://en.wikipedia.org/wiki/Professor

    ያንተም ሆነ የአብረሃም የመልዕክቱ ይዘት ይለያይ እንጂ የመጨረሻ ውጤቱ ወያኔ ሲኖዶስ ስር እንወሸቅ ነው። ከዚህ ቀደም በዚሁ በዘሀበሻ ድረ ገፅ ላይ ስለ አንተ ቤካ አና አብረሃም ከወያኔ የተገባለችሁን ቃል እናንተም በአፀፋው የገባችሁትን ቃል ልታስፈጽሙ በየ ለቅሶ ቤቱ መካራችሁን ስታዩ አንደነበረ በተለቀቀው ጽሁፍ ተረድተናል እናም አሁንም የለቀከው ጽሁፍ የዛው ነጸብራቅ ነው። ለኔ ቢጤ መኃይሙ በመርዝ የተለወስ ማር ለማጉረስ በመሞከርህ ለዛሬው አልተሳከምና ሌላ ብትመክር።

    • Ze Ethiopia,
      Why don’t you put your own idea instead of making meaningless acusations? Everyone is entilted to their opnion. Don’t expect all church members to follow your way of thinking.

      Even though I don’t agree with his opinion, Professor Beka was very rational and polite in his comment.
      I don’t want my side to loose because of this kind of pointless arguments. Therfore, I would suggest you to re-read Mr. Beka’s article and Yantews point of view before showing up to the meeting (If you are member of the church).

      God Bless.

    • Ze’Ethiopia,
      This is meaningless and senseless. Please go back and read what you wrote. You don’t need to value professors with your knowledge. Based on your writing, I can predict that you dropped out from school when you are 5 or 6. Please know who you are write about and what you right about.
      Thank you PROFESSOR Beka and Ato Abraham for doing such a great work. May God bless you and your family.

  3. “Ze Ethiopia”:
    Professor Beka might be doing his Masters at Saint Thomas while teaching undergraduates. For that his students and the respected school calls him Professor Beka Megersa. And our prayers are with him to continue on his Doctorate.

    This message are for all those parishioners of the church that might be confused of what is trying to be accomplished in the Church of Christ. Read with through a calm heart and with prayer.

    Brother Pr. Beka again Kale hiwot yasemalen.

  4. The advice is so good, but I found a lot of contradictory opinions in it. let me say a few points on some of these paradoxical assertions made in the article.
    1. Which structure of the Church are you talking about,my brother? Is it the structure of the church infested by woyane? Or is it the structure we do not know yet? You admitted that they,political people in collaboration with some ‘bishops’ in Ethiopia, dashed the hope of all of us who were yearning to see unity If so, who are we going to be under and united when we join the structure? Anti-peace and anti unity papasat??? What about those who were persecuted?
    2. Is there any structure of E.O.T.C which a single Church has been or be able to under it outside of Ethiopia? One example: The structure of the Church that I know says the head of the ‘sebeka gubea’/board of trustees/ MUST be a priest who is also the head of the Church. But, this regulation can not be applied outside of Ethiopia as the law of America CANNOT allow this to apply. Because, it is only unpaid board of trustees who can be members of the board including the chairman. Our priests,however, are all paid. So, we need a new ‘kalawade’ that has to be prepared specifically for churches outside of Ethiopia considering laws,rules and regulation of foreign countries. Until then, whether we like it or not we are all INDEPENDENT’ and remain the same.
    3. The above point proves us the fact that there are not any churches that are under the structure of E.O.T.C practically and legally. It is only in name that they claim they are under this or that Synod or structure. The common saying ‘This is America!’ works here unconditionally. Every thing has to follow the rule of law and must obey the respective statute of federal and state regulations.Hence, South Dakota or any other Churches that say they are under the structure are not under the Stricture in reality. They are all independent administratively by law.
    4. ‘And eyehonen sinhed papasatum betekirsiteyanin wede andinet yimelisuatal’ ayinet ababl betam yewuahinet new. First who are we uniting with ? Should it not be with those who pray for unity, who look for peace and reconciliation, who alienated themselves from those who are destroying the church, who oppose evil doers and work towards bringing up peace and unity??? Is there any advice in the holy book that says unite with devil and work with him? No,there isn’t! That is why saints preferred persecution to submission to heathens, become martyrs, fought for freedom and liberation as in the case of Abune petros…ETC Therefore, following the foot step of Abune petros starts by saying NO! to those who harm the church and Ethiopia. In my view, those who are saying NO! to be under woyane and its agents are in fact witnessing Abune Petros’s martyrdom, thereby living Christianity in action beyond just words.
    4. Anyway, I strongly believe, that the only solution to this curse of our generation is to unite the fathers. If the reconciliation had been successful, it would have been the best remedy to avoid this kind of scuffle among brothers and sisters. SO,LET US WORK TOGETHER ON THAT EFFORT IF WE ARE GENUINE ABOUT UNITY AND PEACE. Before that happens it is only illusion to see unity in reality.

    • Well said!!! Unlike some of the guys, who tends to label people on the other side as woyanies or irrational, you put valuable point why we shouldn’t and couldn’t be united with the existing Snod.

      I am totaly with you.
      God bless.

  5. In deed it is good idea, but I don.t knew why you take the place of fathawe zama(the person who was in the cross with jess crihist )others, some people think about them or the century when the day off; not all the time. that is the problem we can’t understand each other ato Baka

  6. Dear “Yantew” I applaud you for bringing professionalism to one of the most important topics of our Church today. Let me try to answer your doubts and question with the best of my ability.
    1- Your question was which structure?
    -The structure we are talking about is the one structure of the church that has existed since day one Christianity entered Ethiopia. Even though the full structure (Holy Synod) was fully established about 50 years ago when we were allowed to administer ourselves, the structure of the church always existed whether it was under the Copts or under our own Ethiopian fathers. Through he History of the church we have encountered Kings and bishops who became enemies of the one church. We have encountered era’s where the church barely made it to the next generation. Through all the obstacles and hardship, this church of Christ was able to live of course because it was established through his pure blood. If we even see a current history of the church, we will find the beloved Saint Abune Petros of Ethiopia that faced the hardship of the church and being trustworthy till death. Abune Petros did not align himself with the Fascist nor fathers who were “manifested” by the government. But what you feel to realize my brother is He did not break from the one structure of the church just because some fathers accepted Fascist. We should NEVER compare Abune Petros life of purity and righteous Martyrdom with our actions of being “Independent”
    The LORD still has people under the construction of the church praying and pleading for children like ourselves to STAND UP with them for the this fight. Being Independent and out of the structure only helps our adversary gain power. Our adversary had weakened our power to do NOR bring atleast little change under the structure. The structure WILL FOREVER remain. The current government might not for the next 5 or 10 years, BUT THE CHURCH of CHRIST will forever live through a spiritual structure that passes trough many endurance throughout the era. We should be part of the Spiritual fight of being there for fathers and students of the church who are ought to become the next bishops of the church.

    2- You asked if there is any church in the United States who lives under the structure?
    -Brother, This battle of Unity is not about other churches not being under the structure correctly or not. your question just indicates that we have SO MUCH work to do before handing the church to the next generation. The battle begins with getting rid of a “name” which the church DOES not deserve. The word Independent is NOT the churches language. You might want to continue to use the name thinking you will be fighting the churches enemy with the word, But have you thought about the next generation? have you ever thought about your children and children of your children who will grow with this name that exited almost more than my own age? Do you think your children will define this word with the same way you did. For God’s sake the children who have grown up with me have started to embrace Homosexuality because we are to busy bickering on issues we should have clearly agreed upon if we were truly Unified through the spirit of God.

    4- You said ehenin iyaderegen sinehed papasatum betechristianin wede andinet yimelisutal yimilew ababal “yewahinet new”
    – Brother first of don’t you remember what the lord told his disciples ” take my yoke upon you and learn from me for I am gentle d humble in heart” (Matthew 11:29). so don’t be surprised of Beka is yewah, he’s learning it from his master he worships. (Jesus Christ)
    – Plus what Beka mentioned was if we start Unifying the church pure fathers (Yes they still exist brother) will gain the strength and confidence to confront the government when he interferes with our affairs.

    4- You asked all of us to start to work together:
    -Brother you know the saying “change begins with me”!! We have start to realize that the adversary was able to divide us into millions of pieces because we have opened our doors by establishing entities outside of the One Church Structure. The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church Holy Synod is weakened because o1- Ungoing political interference that continued its cycle from the derg regim until now (which doubled the cause under ehadig).

    Whether we like it or not we have become accomplishers of their agenda by being split into billions of pieces. We must STAND and say NO, the church nor the structure is not “ye weyane” nor Ye “derg” nor any political entity who claims such heresy.

    The battle is long and needs in depth meditation and prayer to fulfill the mission and Unify the church as a whole. But it all begins with us. Since this is a spiritual battle we must get rid of anything that might contradict with the canon of the church. If we ask our fathers to obey the Canons of the church and stand up for the truth, we must be part of the One Structure of the church (get rid of unnecessary politically used word: “independent”) and start fighting the battle with true pure conscious. Saint Paul wrote to Titus telling him ” In everything set them an example by doing what is good” (Titus 2:7)

    Lets be an example and begin the battle to not only Unify our church as a whole but start working with the structure that has existed since day one.

  7. Dn. Ephrem, you need to grow up a little bit and learn a bit more about church administration and unity,etc.1. If you think you are in a church that is not under its mother mother church, then you are not a member of Tewahedo faith let alone to be deacon.
    2.There is not such a thing as abstruct structure of the church that existed for centuries. The first one was the election of 7 people to take care of church and monetary administration by the committee headed by the great martyr, Estifanos. A structure of a church has clear written rules and regulations stipulating the role and responsibility of the committee members. In the case of Ethiopia the ‘kalawade’ For Ethiopian Orthodox Churches in diaspora, there is none! They are established and run their services/ administration/ according to 501c 3, not the kalawade. THEY MUST OBEY THIS REGULATION OF IRS.
    3. We are demonstrating true Christianity by not allying with the enemies of our Orthodox Tewahedo Church and ERthiopia. So we need to follow the foot step of abune petros. What you are saying is joining anti peace bishops and the regimes officials who are also protestants and heathens in their destructive deeds against our Church. Examples: The destruction of Waldiba, Jimma beshahsaAbune gebremenfes kidus, the burning of asebot, ziquaala monasteries,etc
    4.Ye, change begins with self. What kind of change? It should be a change of word and action in standing for unity and with unity loving fathers, not with those so called fathers who foiled peace and reconciliation efforts against prayer, weeping and hope of millions.
    5. You need to come to your senses and dig in the cause and possible way out for this problem, not just echoing what those people and fathers who are part of the problem and aggravating it.
    Hope you come down and contemplate on the issue and avoid unnecessary haggle.

  8. You know brother I thought the message from Beka was enough for you. So I am not going to discuss this further more with you because you tend to put words into my mouth that I or no one said.

    But I will answer only the following for other readers:
    Structure: Yes the structure (mewakir) of the church existed for 2000 years ever since Jesus established it under the 12 disciples. (Matthew 16:18 thats one example) There isn’t a single split second of the Church history that lived outside this great structure. ( I am talking about the Orthodox church)

    When we come to the history of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church we find the same thing. we lived under this structure since the churches establishment. about 50 years ago we were able to administer ourselves with our own born bishops. so brother, there isn’t a single era of the church that the structure never existed.
    ( I keep calling you brother because I know you and I respect you)

    And thank you wedeme I will keep on growing and I pray that I will keep preaching Unity regardless of aging.

    • Ephreme,

      Thank you for your comment. I addmit that I am not familier enough to comment about our church’s organizational structure. To my understanding the church has been “independent” for 20 years for a good reason. Rather than trying to resolve the concerns of many churchs like ours, our church leadership in Ethiopia are adding more reasons thar reinforce our stance. If this is the case, why do we align our church with a leadership that do not live and practice the teachings of our religion.

      Ideally it is good to unit with the party that you have faith in. I am concerned about our church’s capacity to raise her voice for injustice and attacks on other churchs and monasteries. Even if it is going to be a name (‘Independent” label) change, I would say this is not the right time.

      God Bless,

  9. Yantew and Dkn Eph,
    I a bit like your conversations, it has some substance and genuine views compared to some others.
    I see some trickling of understanding directed on the issue compared to some others with mare emotion and frustration.
    So put some life in your conversations with respect, don’t give up or intimidate on each other; you owe to each other and others.
    you all can live with our differences so long as you don’t stretch your skin too much and let issues thrown onto you bust though you.
    You can refer from IRS’s manuals, guides and offices/ officers that IRS don’t regulate religion, but where money comes from and goes to and or on more alike.
    You can also learn from other churches; the Catholics, Greeks etc.
    You will do better!
    Good Luck!

Comments are closed.

Share