የሰለማዊ ትግል ፋይዳ (ከአብርሃ ደስታ)

 

“ምንም ቢሆን ምንም (ለኩፉም ለ ደጉም) ወታደራዊ እርምጃ ተጠቅመህ ስልጣን መያዝ ለኣንድ ወገን ሃሴት ለሌላ ብሶት መሆኑ ኣይቀርም:: ጨቋኙ ደርግ ለሰላማዊ መንገድ ዕድል የሚሰጥ ቢሆን ነሮ ፤ ኣንድነታችን ማስጠበቅ ያልቻለ ኢህወዴግም የጦርነቱ ውጤት የሚያስከትለው ተረድቶ በሰላማዊ ትግል ጨቃኙ ስርዓት ለመጣል ቢችል ነሮ( በነገራችን ላይ ኢህወዴግ እንኳንስ ያኔ ኣሁንም በሰላማዊ ትግል ኣላሸነፈም፤ አረ የሚስበውም ኣይመስለኝም::) ይህ ሁሉ ብሶት ላይፈጠር እሰከዘለዘለሙ ሊያከትም ነበር::

ነገር ግን ለሰላማዊ ትግል ዕድል የማይሰጥ ሃይል መጠቀም ግድ ይላልና ጦርነቱን ኣፋፍመው እርሰ በራሳችን ኣፋጁን:: የተሸነፍነው እኛ ፤ ያሸነፈነው እኛ:: የሞትን እኛ፤ ያለን እኛ:: ጦርነቱ ኣባቶቻችን ና እናቶቻችን ኣሳጣን:: በዚህ ብቻ ኣላቆመም ኣንድነታችን ኣሳጣን:: ( የምን ኣንድነታችን ብቻ ፍቅራችን ጭምር እንጂ::) የጠበቅነው ኣሳጣን ( መብታችን፣ ፍተሃውነት ወዘተ) :: እና ኢህወዴግም በታራው ብሶት ኣሰረገዘን:: በዚህ ኣጋጣሚ እኔም እንደ ኣንድ መሰረታዊ ለውጥ ፈላጊ ስው ኣብራሃና መሰሎቹ የማድረጉት ጥረት ኣደንቃሉሁ::

ሰላማዊ ትግል ኣማራጭ የሌሎው መንገድ ነው ስንል ኢህወዴግን የመሰለ ድርጅት በሃል ኣናሸንፍም ብለን ፈርትን ሳይሆን ሃይል ለሃገርና ህዝብ ሊጠቅም እንደማይችል በማመን፤ እንዲያውም ኢህወዴግ በኛ ተቋዋሚ ፓርቲዎች ሊፈጥሩ የሚችል ኣደጋ እንደ ኪሳራ ሳናስብ ነው:: ገዢዎቻችን ኢህወዴጎች ደሞ በራሳቹ የሰላም መንገድ ኣትዝጉን:: ሰላማዊ ሰልፍ ይፈቀድ:: ተቋዋሚ ፓረቲዎች የልማት ኣጋሮች እንጂ ጠላቶች እንዳልሁኑ ክልብ እመኑ:: የተቋሚ ፓርቲዎች መንገድ ሲዜጋ የህዝብ መብት ና ፍላጎት መንፈግ መሆኑ የሚረዳ የሰከነ ኣስተሳሰብ ይኑርባቹ::

ለፖለቲካ ኣላማ የምትጠቀሙ ሃገር ና ህዝብ የማይጠቅሙ ከንታክንቱ ብልጣብልጥንት ኣቋርጡ:: ከሁሉም በላይ የልማት ቡድን የምትሉ ሽፋኑ ልማት ውስጡ ግን የፖሎቲቻ ካንሰር የሆነ ትስስር ( ፖለቲካዊ ቡድን ) መሆኑ ተከሽፋቹዋልና (ዋጋ እነዳያስከፍላቹ ብየ ነው) ኣሱቡበት::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያ በርግጥ ዴሞክራሲ ይገባታል ወይ?

ሰላማዊ ትግል የማይፈቅድ ሃይልን ለመጥቀም ያስገድዳልና ለሰላም ቅድሚያ እንስጥ!!!”

ሽሻይ ክንፈ ከፃፈው የተወሰደ

1 Comment

Comments are closed.

Share