መላኩ ፈንታ መታመማቸውን ጠበቃቸው ፍ/ቤት ተናገሩ፤ ኦ! ኦ! ርዕዮት ዓለሙ ጡቷን ታማ የጮኸ የለም!

ከሮቤል ሔኖክ

ጀግናዋ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ

ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣውን ሪፖርተር ጋዜጣ ሳነብ ከሰሞኑ ከወረተኛዋ ኢሕአዴግ በፍቅር ሲቆሉ ከከረሙት ባለስልጣናት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ መላኩ ፈንታ ታመው እንደነበር የሚገልጽ ዜና አንብቤ በዜናው ቀናሁ። የሙያ ባልደረባችን ርዕዮት ዓለሙ በጡቷ ላይ እብጠት ወጥቶባት ሕክምና ስትፈልግ፤ ለህክምና ራይድ የሚሆን መኪና የለም ተብላ ወራትን ስትጠብቅ ይህን ዜና እንደዘ-ሐበሻ የመሳሰሉ ነፃ ሚድያዎች ሲዘግቡት እነ ሪፖርተር ሆዬ ጆሯችን አልሰማም ብለው አልዘገቡትም። ዛሬ የአቶ መላኩን ዜና ሲጽፉት ትዝ አለኝና ር ዕዮት ዓለሙ ትዝ አለችኝ። የቅናቴ መነሻም ይሄው ነው።

ስለ ር ዕዮት ዓለሙ የጡት ህመም ለመዘገብ አንጀት ያልነበረው ሪፖርተር ስለ መላኩ ፈንታ መታመመ ጠበቃቸውን ጠቅሶ እንዲህ አለ፦

በተጠረጠሩባቸው የተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ በቁጥጥር ሥር ውለው በእስር ላይ የሚገኙት በሚኒስትርነት ማዕረግ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ መታመማቸውን ጠበቃቸው ግንቦት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው አስታወቁ፡፡

ጠበቃው አቶ መላኩ በአስቸኳይ ሕክምና እንዲደረግላቸው ጠይቀው፣ “እኚህ ሰው በጠና ስለታመሙ የታሪክ ተወቃሽ እንዳንሆን፤

የአቶ መላኩን ጤንነት በሚመለከት ጠበቃው በዝርዝር ጠይቀው የሕመማቸው ዓይነትና ደረጃ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ባይረዱም፣ መልካቸው ቢጫ ሆኖ እንዳዩዋቸው ገልጸዋል፡፡ ለምን እንዳላነጋገሩዋቸው ሲጠየቁ በቂ ጊዜ እንዳልነበራቸው የገለጹት ጠበቃው ከእሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን፣ ነገር ግን ሆስፒታል ይሂዱ ወይም አይሂዱ አለማወቃቸውንም አስረድተዋል፡፡

በአጃቢ ሆነው ሕክምና እንዲያገኙ ጠበቃው ላነሱት ጥያቄ፣ ስለመታመማቸው የሚገልጽ ማስረጃ ከክሊኒክ ወይም ከሆስፒታል እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ያለማስረጃ ትዕዛዝ መስጠት እንደማይቻል ፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

አቶ መላኩ መንግሥት የሚያውቀውና በአገር ውስጥ ሕክምና የማይድን ሕመም እንዳለባቸውና በውጭ አገር እየታከሙ እንደነበር፣ ለፍርድ ቤቱ ራሳቸውና ጠበቃቸው ማስረዳታቸው የሚታወስ ነው፡፡ ” ብለዋል

አንድ በሙስና የበሰበሰና የሰዎች ሰብአዊ መብት ሲገፈፍ አቤት ሳይል የከረመ ሆዳም ባለስልጣን ምንስ ቢሆን የምን ታሪክ ይመጣል? ይልቅ የታሪክ ተወቃሽ የሚያደርገን የመናገርና የመጻፍ መብቷን ተገፋ ታስራ ህክምናም እንዳታገኝ በወህኒ የተወረወረችው ር ዕዮት ጉዳይ ነው የታሪክ ተወቃሽ ሊያደርግ የሚችለው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቪ ኦኤ ወይስ የኢትዮጵያ/ወያኔ ሬዲዮ ?

 

መላኩ ፈንታ እኚህ ናቸው።

እኔን የገረመኝ ከሰሞኑ በስርቆት ወንጀል የታሰሩት እነዚህ የወያኔ ተላላኪዎች በፍርድ ቤት ‘ይታዘንልን’ ሲሉ ያቀረቡት ማስተዛዘኛ ሁሉ ህመምን ነው።

– አንዱ የልብ ህመም

– አንዱ መናገር የማልፈልገው በሽታ

– አንዱ ሌላ

– ሌላው ሌላ በሽታ ጠርተዋል: ርዕዮት ዓለሙ ጡቷን ታማ ሲሳለቁ፤ ውስኪያቸውን ሲጨልጡ የነበሩ ተላላኪዎች  ይህን “ይታዘንልን?” ምክንያት ሲያቀርቡ እኛ እንቀበል ይሆን?

 

 

 

4 Comments

  1. Ante demo min yemeluk kizebe neke ebak? So the lawyer of Reyot Alemu can tell the court that she is sick! What that has to do with the sickness of Melaku? are you saying he do not deserve a relief from his illness-which should be granted to Reyot Alemu? yehonk bisbis nek! Chigirik ke reporter gar yimeslal-yan weyane gazetenja dewilek mikinyatun teyek!

  2. Dear writer
    please go to Addis Abeba and Help her…she, Reot needs help
    politic is not a religion.Robel Henok when you will be at her side
    she will be happy….play christian…or freedom fighter

  3. ኢንጂነሩ የወያኔ ሰለባ ከመሆን አመለጠ። በካናዳ የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ አቀረበ። ከፋሲል ፈንታ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ
    ከልሳነ ህዝብ ዘጋቢ
    ባገራችን ምርጫ በተቃረበ ቁጥር የሚታየው ውጣ ውረድ ከተለመደ ውሎ አድሯል። ወደ 400 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ከሰማያዊ ፓርቲ ጎን ተሰልፈው ተመራጭ ለመሆን በተመዘገበቡበት ባሁኑ ወቅት መንግስት አንዳንድ ኢንፎርሜሽኖችን ለማፈን ያማያደርገው ጥረት የለም። ለእጩነት ከቀረቡት ውስጥ ከግማሽ በላይ ታስረውና ተሰቃይተው በዋስና በማስፈራሪያ ሲለቀቁ በርካታዎችም የገቡበት ሳይታወቅ ቀርቷል። ለምርጫ ዕጩ ተብለው ለመንግስትና ለህዝብ ይፋ ከመደረጋቸወፀ በፊት በተካሄደው ከፍተኛ ርብርብ ወያኔ በርካታዎቹን በጠዋቱ ሰለባ እንዲሆኑ በማድረግ ስራውን በተገቢ መንገድ ማከናወኑን ለማወቅ ተችሏል።
    በሌላ በኩል ደግሞ በወያኔ የታገዱትን ዌብ ሳይቶች በሙያህ ተጠቅመህ ተቃዋሚዎች እንዲያዩዋቸው አድርገሃል በሚል ክስ ኢንጂነር ፋሲል ፈንታን በፖሊስ ቁጥጥር ስር በማዋል አስሮ፣ አሰቃይቶና ማስፈራሪያ አስፈርሞ በዋስ ቢለቀውም ባገር ውስጥ ከቆየ ደግመው ሰለባ እንዳያደርጉት በመስጋት በካናዳ የፖሊቲካ ጥገኝነት ጠየቀ።
    ፋሲል ፈንታ የሰማያዊ ፓርቲ አባል በመሆን በመኖሪያ ወረዳውና በፓርቲው ዋና መስሪያ ቤት ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደነበረ ለማወቅ ተችሏል። ፋሲል ሪፖርተራችን በስልክ ያወያየውን በሚከተለው መልኩ መልስ ሰጥቶበታል።
    ል/ህ ፡- አቶ ፋሲል አሁን ባለህበት ሁኔታ ላይ ሆነህ የስልክ ቃል ምልልስ ለማድረግ ፈቃደኛ በመሆንህ በጣም አመሰግናለሁ።
    አቶ ፋሲል፡- ምንም አይደል። እኔም ቃለምልልስ እንድሰጥህና ባገራችን በገዢው ፓርቲ አማካኝነት እየተከናወነ ያለውን ሴራ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን ጥረት በማድረግህ ከፍ ያለ ምስጋና አቀርብሃለሁ።
    ል/ህ ፡- በመግቢያ ውይይታችን ጊዜ ስለራስህ ብዙም መናገር እንደማትፈልግ ስላሳሰብከኝ በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ልግባ። በፓርቲው አባልነትሀ የታገዱ ዌብ ሳይቶችን ሊንክ እየፈጠርክ ለተቃዋሚዎች አክሰስ ትሰጥ ነበር የሚለው ውንጀላ ባጠቃላይ አውነት ነው ወይስ አይደለም?
    አቶ ፋሲል፡- በመጀመሪያ እንዲህ ዓየነቱ ውንጀላ ሊቀርብብኝ የቻለው የኮምፒውተር ባለሙያ ስለሆንኩኝና እንደዛ የማድረግ ሙያዊ ብቃቱ እንዳለኝ ስላወቁ በሰማያዊ ፓርቲ መታቀፌም ራስ ምታት ሆኖባቸው ሊሆን ይችላል። የኮምፒውተር ሳይንስ ባለሙያ ባልሆን ኖሮም ለኔ የሚመጥን ሃሳብ ፈጥረው ሊወነጅሉኝ ይችሉ እንደነበር መገመት አያዳግትም። ለዚህኛው ጥርጣሬ መዳበር ደግሞ የራሴ የሆነ ስህተትም አለበት። ባጠቃላይ ግን እንደ ፓርቲ ስራ ሙሉ በሙሉ የታገዱትን ዌብ ሳይቶች ፕሮክሲ ሰርቨር በመፍጠር የተወሰኑ የሚቀርቡኝና መንግስት ተቃዋሚ ብሎ በጥላቻ የሚያያቸው ሰዎች አክሰስ እንዲያገኙ አድርጌ አውቃለሁ።
    ል/ህ ፡- የራሴ ስህተትም አለበት ስትል ምን ዓይነት ስህተት ነው እሱ?
    አቶ ፋሲል፡- ከመታሰሬ ጥቂት ቀናት በፊት ንብረትነቱ የቤተሰቤ በሆነ ካፌ ውስጥ ለማምነው ሰው ከታገዱት ዌብ ሳይቶቸች ያገኘሁትን ሁለት ገፅ ኢንፎርሜሽን አትሜ ሰጥቼው ነበር። አሁን ሳስበው ያንን ሰው ማመን አልነበረብኝም። ፓርቲውን እንደ ፓርቲ ግን አክሰስ እንዲያገኝ ያደረግኩበትም ሆነ የተጠየቅኩበት ጊዜ የለም።
    ል/ህ፡- አሁን ፖለቲካ በቃህ መታገል አቆምክ ማለት ነው?
    አቶ ፋሲል፡- ፖለቲካ ባደጉት አገሮች ህዝብን የምታገለግልበት መሳሪያ ነው። በኛ አገር ደግሞ ፖለቲካ ህይወትህ ውስጥ ሳትፈልገው የሚመጣ ክስተት ስለሆነ ወደድክም ጠላህም ከፖለቲካ ነፃ መሆን አትችልም። የፓርቲ አባል ልትሆንም ላትሆንም ትችላለህ። በያንዳንዷ ቀን ግን የፖለቲካው ግድፈት በህይወትህና በቤተሰብህ ህይወት ላይ የአጭር ጊዜም ይሆን የረዥም ጊዜ ለውጥ ማምጣቱ የማይቀር ነው። እኔ ለጊዜው ሊደርስብኝ ከሚችለው ልቋቋመው የማልችለው አደጋ ለማምለጥ እንጂ ከትግል ለመሸሽ አይደለም ወደ ስደት ያመራሁት። እኔና መሰሎቼ ከፖለቲካዊ ትግል እራሳችንን ካገለልን ማን መጥቶ ነው ህዝባችንን ነፃ የሚያወጣልን እኛ ድምፃቸው ለማይሰማ ሚልዮኖች ለመታገል ከፈራን ጭቆናንና አፈናን ተቀበልን ማለት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ አሁን ካለበት የተወሳሰበ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ ነፃ እስካልወጣ ድረስ መታገሌን አላቋርጥም። ይህም ስልህ በሰለጠነና በሰላማዊ መንገድ የሚደረውን ትግል ነው። ጭቆናንና አፈናን እሺ ብለን በዝምታ ከተቀበልን የመጣውን ሁሉ የምንችል አህዮች ሆንን ማለት ነው። ያ በደልና ግፍ አንድ ቦታ ላይ መቆም አለበት ብለን የምናምን ከሆነ ደግሞ የማቆሚያው የመጀመሪያው መሰረት መጣል ያለበት አሁን ነው። ስለዚህ ላገሬ ህዝብ ነፃነት ይጠቅማል ባልኩት ርእስ ላይ በሰላማዊ መንገድ ትግል ለማድረግ የሚቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ።
    ል/ህ ፡- በውጭ ሃገር ያሉ ተቃዋሚዎች የሚያደርጉት ትግል በኢትዮጵያ ያለውን የፖለቲካ ሁኔታ በመለወጥ ረገድ ያላቸውን እሰተዋፅኦ እንዴት ታየዋለህ? አንዳንድ ሰዎች በውጭ ያሉ የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዋሚዎች ከመጮህና መጥፎ ዜና ከማሰራጨት የዘለለ ጠቀሜታ የላቸውም ሲሉ ይተቿቸዋል። አንተ እንደ በሳል ፖለቲከኛ ይህን አባባል እንዴት ታየዋለህ?
    አቶ ፋሲል፡- በመጀመረያ እኔ እንደ ግለሰብና እንደ ሰማያዊ ፓርቲ አባል ስለ ፍትህ የሚጮህ እንጂ ጥይት የሚተኩስ አሊያም ድንጋይ የሚወረውር ተቃዋሚ እንዲኖር አልፈልግም፡ አልደግፍምም። እኛ ባገር ቤት የምንከተለው ሰላማዊ የተቃውሞ መንገድ ስለተከተሉና ወርቃማ ጊዜያቸውን ለህዝብ ጥቅም ስላዋሉ የሚተቿቸው ሰዎች መኖራቸውም በራሱ መልካም ነው። ጥቅም የሌለው እኮ አይተችም። ምንም ሃይልና መልእክት ያለው ስራ ባይሰሩ ኖሮ ሊያውቋቸውም አይችሉም ነበር። እኔ ለነዚህ የዳያስፖራ ተቃዋሚዎች ያለኝ ከበሬታ ከፍ ያለ ነው። ፓርቲዬ ሰማያዊ ፓርቲም ከዚሁ የተለየ አመለካከት ሊኖረው እንደማይችል እርግጠኛ ነኝ። ምክንያቱም ይህ ጥያቄ በመሰረቱ የመርህ ጥያቄ ስለሆነ የነዚህ ተቃዋሚዎች መኖር በራሱ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው እንጂ ሊጣጣል ወይም ሊኮነን የሚገባው አይደለም። አካሄዱ ላይ ስህተት ካለ ስህተቱን ማሳየት እንጂ በደፈናው መፈረጅ ጤነኛ አመለካከት ካለው ህሊና ሊመነጭ አይችልም። ምናልባትም እንደዚያ ያለ የፕሮፖጋንዳ ስራ ከመንግስት ደገጋፊዎች በኩል የሚሰነዘር የማጥላላት ዘመቻ ሊሆንም ይችላል። ዋናው ነገር ስራ እየሰሩ ነው። ስራቸው መናኛ ቢሆን ኖሮም ያን ያህል የመንግስትና የተቺዎች ትኩረት ሊስብ ባልቻለ ነበር።
    ል/ህ ፡- አመሰግናለሁ አቶ ፋሲል። አሁን ወዳገርቤት ልመልስህና መጪው የግንቦት ምርጫ ውጤት ምን ሊመስል እንደሚችል ካሁኑ መተንበይ ይቻላል?
    አቶ ፋሲል፡- እንደ ፓርቲ ሳይሆን እንደግለሰብ የራሴን አስተያየት ልሰጥሀ እችላለሁ። ውጤቱ በሁለት ደረጃ ተከፍሎ የሚታይ ይሆናል። ለመንግስትና ለደጋፊዎቹ የሚኖረው እንድምታና ላለም አቀፍ ኅብረተሰብ የሚኖረው ትርጉም እንዲሁም ተቀባይነቱ ነው። ውጤቱ የወያኔ መንግስት አሸነፈ በሚል የሃሰት ጋጋታ እንደሚታጀብ ከወዲሁ የታወቀ ነው። ምክንያቱም ፍትሃዊ ውድድር በሌለበት ምርጫ ማን ሊያሸንፍ እንደሚችል መገመት የፖለቲካል ሳይንስ አዋቂ መሆንን አይጠይቅም። ወያኔ ከመጀመሪያው የተቃዋሚ ፓርቲዎች እጩዎችን ለህዝብና ለደጋፊዎቻቸው እንኳ ይፋ ሳይሆን በየእስርቤቱ ማግዶና አሰቃይቶ ካገር እንዲሰደዱ ያልቻሉት ደግሞ ልሳናቸውን እንዲዘጋ አድርጓል። የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች ምርጫው ሳይቃረብ በጠዋቱ ከእይታ ውጭ በተደረገበትና በርካታ ማጭበርበር በሰፈነበት የሃሰት ምርጫ ተቃዋሚዎች ድል ያደርጋሉ ብሎ ማሰብ የማይመስል መላምት ነው። ይሁን እንጂ እንዳንድ ተቃዋሚዎች በአለም አቀፉ ኮሚኒቲ ድጋፍና ክትትል ለስልጣን ይበቁ ይሆናል። ይህ ሲሆን በራሱ ታላቅ ድል ነው። ሃምሳ የሚሆኑ የተለያየ አመለካከት ያላቸው ፖለቲከኞች ወደ ፓርላማ ገቡ ማለት ትልቅ እመርታ ነው። አየህ ዲሞክራሲና ፍትህ ለማምጣት ረዥም ሂደት ውስጥ መጓዝን ይፈልጋል። በዚህ መልኩ ለሚረዳው ሁለት ወንበር ማሸነፍም ትልቅ ድል ነው። ለውጥ በአንድ ሌሊት የሚፈነዳ እንጉዳይ መስሎ ለሚታየው ሰው ደግሞ ስሜትም ላይሰጠው ይችላል። ስለዚህ እኔ የማየው ከዚህ አንፃር ነው።
    ል/ህ ፡- አቶ ፋሲል ከቃለ መጠይቁ በፊት ስናወራ ያየሁብህ ጥልቀት ያለው የፖለቲካ ግንዛቤ እኔን እራሴን መልሼ እንድመረምር ያነሳሳኛል። እስቲ በርካታ የፖለቲካ ሰዎች የሚከራከሩበት አንድ ፅንሰ ሃሳብ ላይ ያለህን አመለካከት ልጠይቅህ። አንዳንድ ፖለቲከኞች ህዝብ ወደ እውነት መምጣት አለበት ሲሉ አንዳንዱ ደግሞ እውነት ወደ ህዝብ እንጂ ህዝብ ወደ እውነት መምጣት የለበትም ሲሉ ይደመጣሉ። እንተ ከየትኛው ሃሳብ ጋር ነው የምትወግነው?
    አቶ ፋሲል፡- በመጀመሪያ ታሪክ ሰሪው ሰፊው ህዝብ ነው የሚል ሁሉም የሚስማሙበት መፈክር ወይም አባባል አለ። ታሪክ የሚሰራው የነቃ፣ የተደራጀና የታጠቀ ህዝብ ብቻ ነው የሚሉ ደግሞ አባባሉን በደፈናው እንዳንቀበለው ይነግሩናል። እኔም ያልነቃ፣ ያልተደራጀና በቂ ንቃተህሊናዊ ትጥቅ (Psychological readiness) የሌለው ህዝብ ታሪክ ሊሰራ ከማይችልበት ሁኔታ አልፎ መጥፎ አመለካከት ለሚከተሉ ጥቂት ሰዎች መሳሪያ በመሆን ሊያገለግልም ይችላል የሚል እምነት አለኝ። ያም ተባለ ያ ግን የህዝብን የበላይነት ከተባሉት አስተሳሰቦች ባሻገር ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ሳንቀበል ዲሞክራሲያዊ ስርአት መገንባትም ሆነ ፍትህን ማስፈን አንችልም ብዬ አምናለሁ። ህዝብ እንዲነቃና እንዲደራጅ የሚከፈለውን መስዋእትነት መክፈል እንጂ ህዝብን በማንኛውም ደረጃ መፈረጅና የራስን ድርሻ ላለመታገል እንደ “excuse” ማቅረብ ጠቀሜታ የሌለው የሰነፎች መርህ ነው። ኮሚኒስቶች ህዝባዊ ውሳኔ ላለመሻት የሚጠቀሙበት ሌኒን ያስተማራቸው ጥቅስ ይጠቀማሉ። “ አንዳንዴ ህዝብ ፀረ መብቱ ይታገላል” በማለት ህዝብንና የህዝብ የበላይትን ዝቅ ለማድረግ ይሞክራሉ። በነገራችን ላይ ህዝብ ማለት የነጠላ ሰዎች (individuals) ስብስብ ስለሆነ የያንዳንዱን ግለሰብ ስብእናን ማእከል ያላደረገ ህሊና ላይ ተመስርቶ ስለ ህዝብ የሚሰጠው ጥቅል አስተያየት አብዛኛውን ጊዜ በመርህ ደረጃም ስህተት (Wrong in Principle) ተብሎ ሊታለፍ ይገባል። ሌላኛው ነጥብ (factor) ደግሞ ስለህዝብ አቋም ለመያዝ የምታይበት እውነታ ነው። ለምሳሌ በሙሉ ህሊናና ሞራላዊ ብቃት ለህዝብ ጥቅም ቢሰሩ የመንግስት አካላት በኩል በተጠኑና በፍፁም ለህዝብ ጥቅም ሲባሉ በሚወሰዱ እርምጃዎች ላይ ማህበራዊ ይሁንታ (Social accord) ሳያስፈልግ ወደ ውሳኔ ሊገቡ የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። ለዚህም ነው ዲሞክራቲክ በሆኑ አገሮች መንግስት አንዳንዴ ህዝብ የሚቃወማቸው የሚመስሉ ውሳኔዎችም ጭምር በድፍረት ለማሳለፍ የሚነሳሱትና የሚያስተላልፉት። ለነገሩ በዲሞክራቲክ አገራት መንግስትን የሚመሩት ሰዎች ህዝቡን ወክለው ለመስራት በምርጫ ስልጣን ላይ የወጡ ስለሆኑ ያን ያህል ተቃርኖ አያጋጥምም።
    ል/ህ ፡- አሁን እንግዲህ በመግቢያችን እንዳሳሰብከኝ መጠንቀቅ ያሉብኝ ጉዳዮችን ግምት ውስጥ በማስገባት ከመሰናበታችን በፊት ማስተላለፍ የምትፈልገው መልእክት ካለ እድሉን ልስጥህና እንሰነባበት።
    አቶ ፋሲል፡- በመጀመሪያ ለዚህ ለልሳነ ህዝብ እንግዳ አድርገህ ቃለ መጠይቅ ስላደረክልኝ በጣም አመሰግናለሁ። ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ የምፈልገው መልእክት ግን የመንግስት ተቃዋሚም ሁኑ ደጋፊዎች አሁን 21ኛ ክፍለ ዘመን ላይ ነው የምንገኘው። እራሳችንን ከዓለም ጋር በመልካም ሁኔታ አቆራኝተን ልጆቻችን በሰላምና በብልፅግና የሚኖሩባት አገር ለመፍጠር ብቸኛው መንገድ የዲሞክራሲና የፍትህ የበላይነትን የሚቀበል ህዝባዊ መንግስት በመመስረት ብቻ ነው። ላለፈው በደላችን ይቅር ተባብለን ወደፊት የምናይበት ጎዳና አሁን መምረጥና መትከል ካልቻልን ለወደፊት አሁን የምናስብላት አገር ህልውናም አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል። ይህ የእውቀት ሳይሆን የህልውና ጥያቄ ነው። ስለዚህ ላፍታ ቆም ብለን ስለመጪው የኢትዮጵያ ሁኔታ እንድናስብ በትህትና እጠይቃለሁ።
    ል/ህ፡- የልሳናችን ታዳሚዎች በቀጣይ ከኢንጂነር ፋሲል ፈንታ ጋር ሰፊ የሆነ ቃለ ምልልስ ይዘንላችሁ እንቀርባለን። ለዛሬው የነበረን ቃለምልልስ በዚህ ላይ ያበቃል። ቸር እንሰንብት።

  4. ሰማያዊ ፓርቲን በመወከል የምርጫ ታዛቢ ሊሆኑ የነበሩት ለስደት ተዳረጉ።
    ከወ/ሮ መንበረ ተክለማርያም ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ—ክፍል ፩
    ከልሳነ ህዝብ

    ወ/ሮ መንበረ ተክለማርያም ይባላሉ። ተወልደው ያደጉት በአዲስ አበባ ከተማ ነው። ባለትዳርና የሶስት ሴት ልጆች እናት ናቸው። ሰማያዊ ፓርቲ ከምስረታው ጀምሮ በአባልነት ያገለገሉና በማንኛውም ሁኔታ እውነትን ለመናገር የማይፈሩት ጠንካራ ተቃዋሚ ሰሞኑን ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ወደ ካናዳ በመጓዝ የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ስንሰማ ካለንበት በስልክ ቃለ ምልልስ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው።
    ወይዘሮ መንበረ ካለምንም ማቅማማት ከኛ ጋር ቃለ ምልልስ ለማድረግ ፈቃደኛ በመሆናቸው በዝግጅት ክፍላችንና በመፅሄታችን አንባበዎች ስም ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላቸዋለን።
    ል/ህ፡ ወ/ሮ መንበረ ከተለመደው አጠያየቅ ወጣ ባለ መልኩ ጥያቄ ላቀርብልዎት ነው የፈለግኩት ምን አስተያየት አለዎት?
    ወ/ሮ መንበረ፡ እኔ ምን ቸገረኝ? ጠያቂው አንተተ ነህ፡ መላሿ ደግሞ እኔ። የማውቀው ነገር ከጠየቅከኝ እመልስልሃለሁ፡ ከከበደኝ ደግሞ ይለፈኝ እልሃለሁ።
    ል/ህ፡ መልካም። እርስዎ እራስዎትን አንዴት ነው የሚገልፁት? ማለትም ከፖለቲካ ህይወትዎ ጋር በተያያዘ መልኩ እራስዎትን ሲገልፁት እንዴት ያስቀምጡታል?
    ወ/ሮ መንበረ፡ በመጀመሪያ እራሴን እንደ ፖለቲከኛ አይቼም አስቤም አላውቅም። መጀመሪያ የፍትህና የዲሞክራሲ መጓደል በሽታ ለዘመናት በተጠናወታት አገር ሰለተፈጠርኩ ለህዝብ የሚገባ መብት መነፈግ የለበትም ብዬ እምርሬ መታገል በመጀመሬ እንደ ፖለቲከኛ ታየሁ እንጂ እኔ እራሴ የፖለቲካ ሰው ለመሆን ብዬ የተራመድኩት አንድ እርምጃም የለም።
    ል/ህ፡ ዞሮ ዞሮ ግን እርስዎ በመንግስት ላይ በቀጥታና በግልፅ ትችት በመሰንዘር አዲስ አበባ ከተማ በወረዳዎ ታዋቂ ነዎትና ፖለቲከኛ ሆኑ ማለት አይደለም እንዴ?
    ወ/ሮ መንበረ፡ እንተ እንደፈለግክ ግለፀው፡ እኔ ግን ሁሉም ሰው የሌላውን ሰው መብት እስካልነካ ድረስ የመሰለውን ሃሳብ ካለምንም ፍርሃትና መሸማቀቅ መግለፅ የእግዚአብሄር ስጦታ የሆነ መብቱ ነው። ፍትህን የማግኘት የተፈጥሮ መብት በሰዎች አማካኝነት መከልከል የለበትም በማለት ይህንን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመቃወም ማድረግ ያለብኝ ከዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ጋር በመወገን ሰላማዊ ትግል ማካሄድ ስለነበረ ነው ሰማያዊ ፓርቲን ከመጀመሪያው ጀምሬ የተቀላቀልኩት።
    ል/ህ፡ ከሰማያዊ ፓርቲ በፊት ለምን በሌላ ፖለቲካ ፓርቲ አልታቀፉም ነበር?
    ወ/ሮ መንበረ፡ መጀመሪያ ወያኔ የሚባለው መንግስት የተሳሳተ የጎሳ ፖለቲካ ይዞ ሲመጣ በየስብሰባው ልክ እንዳልሆነ ተነስቼ ህዝብ ፊት እናገር ነበር። በሁዋላ በርካታ ሰዎች ሰለባ እየሆኑ ሲመጡ በወያኔ ጠሪነት በሚከናወኑ የህዝብ ስብሰባዎች መገኘቴን ቀነስኩ። በህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል ግን ከቀን ወደ ቀን እየከፋ ሄደ። ቀደም ባሉት ጊዜያት ቀርቦ ስለ ሰላማዊ ትግል ያወያየኝ ሰው አልነበረም፡ ምናልባትም እስካሁን አባል ሳትሆን አትቀርም ከሚል አመለካከትም ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለኝ።
    ል/ህ፡ ስለፖለቲካው ወደኋላ እናቆየውና እርስዎ የቤተሰብ ሃላፊና የሶስት ሴቶች ልጆች እናት ሆነው ጎን ለጎንም ደግሞ የንግድ ስራ ያከናውናሉ፡ እንደሚወራው ከብዙ አባላት በተለየመልኩም አንዳንድ ሃይማኖተኞች ቤት ለቤት እየዞሩ እምነታቸውን እንደሚሰብኩት ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ለሰዎች ይመሰክሩ ነበር ይባላል። እነዚህን ተግባራት ለማከናወን ደግሞ ጊዜ ያስፈልጋል። ወ/ሮ መንበረ 25 ሰዓት ያለው ቀን ነው ያላቸው የሚለው የሚያውቋቸው ሰዎች ትችትን እንዴት ነው የሚያዩት?
    ወ/ሮ መንበረ፡ ያን ያክል ባይጋነንም time management ላይ ጥሩ ተሰጥኦ ሳይኖረኝ አይቀርም። ምናልባት በርካታ ስራዎች በአንድ ቀን ስለማከናውንና አንዳንዴም ስለሚሳካልኝ ይሆናል። ለዛሬ ያሰብኩት ዛሬውኑ ለማከናወን እጥራለሁ። ምክንያቱም ነገ የራሱ የሆነ ሌላ task ይዞ ነው የሚመጣው። እነዛ የተባሉት ሃላፊነቶች እርግጥ ነው በተቻለኝ አቅም አጣጥሜ ለማከናወን እሞክራለሁ። ብዙ ሰው አንድ ከበድ ያለ ስራ ካከናወነ ቀኑን በሙሉ ሊያሰራው የሚችለውን energy አልቋል ብሎ ያምንና ለዛሬ ያከናወንኩት ብዙ ነው ብሎ ለሌላ ቀን ቀጠሮ ይይዛል፡፡ እንደዚያ ማድረግ በራሱ የሰው አስተሳሰብ የወለደው ድክመት ነው። እኔ እንግዲህ በጣም የተለየና ብርቅ የሆነ ችሎታ ባይኖረኝም እንደነገርኩህ ጊዜዬን በደንብ ነው የምጠቀምበት።
    ል/ህ፡ ከአሜሪካ ጉዞዎ መልስ አዲስ አበባ ላይ ታስረው እንደነበር ሰማን፡ ይህ የሆነው ለምንድነው?
    ወ/ሮ መንበረ፡ እንዲህ ዓይነቱ ነገር እንኳ በግላችን ብናወራው ነበር መልካም፡ ንገሪኝ ካልክ ግን ያው መንግስት ማንንም ስለማያምን በራሴ ማለትም በቤተሰብ ጉዳይ ሄጄ ስመለስ በአሜሪካ ከተቃዋሚዎች ጋር ለመገናኘትና ለሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ለማሰባሰብ ነው የሄድሽው በማለት ነበር ችግር የፈጠሩብኝ።
    ል/ህ፡ ስለ መታሰርዎ ህዝብ ቢያውቀው ምን ገዳት አለው?
    ወ/ሮ መንበረ፡ አየህ የኔ መታሰር በአገራችን ካለው ተጨባጭ ሁኔታ ሲታይ በጣም የሚያስደነግጥና የሚያስገርም ክስተት ስላልሆነ ነው። በርካታ ሺዎች ኢትዮጵያውያን አሁን በዚች ደቂቃም ጭምር በየእስር ቤቱ በሚሰቃዩበት ሰዓት ስለራሴ ባወራ ግብዝ የሆንኩ ስለሚመስለኝ እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም። ስለራሴ ሳወራ መናገር ለማይችሉት ፍትህ ፈላጊ ወገኖቼ ሳልናገር እንዳልቀር እንጂ ስለራሴ ለመናገር ካለመፈለግ አይደለም። እናንተ እንግዲህ ልሳነ ህዝብ ነን የምንባለው ብለኸኝ የለ ስለሳራችሁ ሳይሆን ስለሌሎች ነው የምትናገሩት። እኔም የመናገር መብት ለተነፈጉት ወገኖቼ ብናገር ነው በጣም ደስ የሚለኝ።
    ል/ህ፡ ገባኝ። አሁን በካናዳ የፖለቲካ ጥገኝነትቶ ጥያቄ እንዳቀረቡ ነው የሰማሁትና ወደፊትስ በምን ዓይነት መንገድ ነው የጀመሩትን ሰላማዊ ትግል ማስቀጠል የሚፈልጉት?
    ወ/ሮ መንበረ፡ እኔ አሁን ባለሁበት የሰለጠነ ማህበረሰብ ስለወገኖቼ በደልና ጥቃት ከመናገርና ሌሎች በርካታ ኢትዮጵያውያን
    ከሚያካሄዱት ሰላማዊ ትግል በመቀላቀል በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ዓለም አቀፍ ጫና የሚካሄድበትን መላ አፈላልጋለሁ። እዚሁ ከመጣሁ ጀምሮ እንኳ ላገኘሁዋቸው ኢትዮጵያውያና ካናዳውያን ስለሃገሬ ተጨባጭ ሁኔታ በመንገር ድጋፍ እንዲሰጡ ስነግራቸው ነው የሰነበትኩት። አቅሜ ሲፈቅድ ደግሞ ከዚያ በላይ ለማድረግ ሃሳብ አለኝ።
    ል/ህ፡ በወረዳዎ ለምርጫ ተወዳዳሪነት ሃሳብ ቀርቦልዎት እምቢ ማለትዎ ስሰማ በጣም ነበር የተገረምኩት። ለምንድነው ለመመረጥ ፈቃደኛ ያልሆኑት?
    ወ/ሮ መንበረ፡ እኔ በወረዳዬ እንድወዳደር የመጀመሪያው criteria ሆኖ የቀረበው ፖለቲካዊ ብቃቴ ሳይሆን በምኖርበት አከባቢ በህዝብ ዘንዳ ያለኝ ተቀባይነት ብቻ ግምት ውስጥ ያስገባ አካሄድ ነበር። ያ አደገኛና ለምወክለውም ሆነ ለራሴ ጠቀሜታ የሌለው አስተሳሰብ ስለነበር ነው እኔ አልመጥንም በማለት ዕጩ የመሆን ጥያቄውን ያልተቀበልኩት። እራሴን ለማታለል ካልሆነ በስተቀር እኔ ጥልቀት ያለው የፖለቲካ ዕውቀትና በህዝብ ፊት የተቀነባበረ ንግግር የማድረግ ችሎታ የለኝም። አቅምህን ማወቅ በራሱ እኮ ትልቅ ነገር ነው።
    ል/ህ፡ ብዙ ሰው ፓርላማ መግባት እንደ ሹመት ስለሚያየው ደስተኛ ሆኖ ነው ዕጩነቱን የሚቀበለው፡ እንደውም አንዳንድ ቦታ ላይ እኔን ይገባኛል በማለት ሌላ ሰው ሲታጭ የሚያኮርፉ ሰዎችም አሉ። የርስዎ ስሳኔ ደግሞ ከዚሁ ከተለመደው አካሄድ የተለየ ነውና እንዴት ይገልፁታል?
    ወ/ሮ መንበረ፡ አኔ እራሴን ነው የማስበው፡፡ ምናልባት ፖለቲካዊ ብቃቱ እንዲሁም የስነ ልቦና ዝግጅቱ ቢኖረኝ ኖሮ እኔም ይገባኛል የማልልበት ምክንያት አይታየኝም። እኔ የራሴን ጥንካሬዎችና ድክመቶችን በደንብ ነው የማውቃቸው። በዚሁም መሰረት የማይመጥነኝ ክብደት ልሸከም በማለት እራሴን መጉዳት አልፈልግም። ባገራችን የዲሞክራሲ ባህል ባይኖርም ባደጉት አገሮች የሚደረጉ የፖለቲካ ስልጣን ውድድሮችን አልፎ አልፎ በቴሌቪዥን አያለሁ። እነዛ አገሮች የደረሱበት ደረጃ ላይ ስላልደረስን መወዳደር ማለት አብዛውን ጊዜ በአደገኛ ፍፃሜ ላይ የተመሰረቱም ስለሆኑ እንዲሁ ጥልቅ የሚባልበት አይሆንም።
    ል/ህ፡ ወደ አገራቸችን ኢኮኖሚ ልውሰድዎትና፡ የኢትዮጵያ መንግስት ያገሪቱ ኢኮኖሚ በያመቱ በሁለት ዲጂት እያደገ ነው፡ በማለት ሲለፍፍ ይሰማል። እርስዎ ይህንን አባባል እንዴት ያዩታል?
    ወ/ሮ መንበረ፡ በመሰረቱ እኔ አካውንቲንግ እንጂ ኢኮኖሚክስ ሰላላጠናሁ ስለ ኢኮኖሚ ማደግም ሆነ አለማደግ የአሃዝ መረጃ በማቅረብ ላስረዳ አልችልም። እንደዛ ባደርግም አላስፈላጊ ድፍረት ስለሆነ። እኔ ጥያቄህን መመለስ የምችለው እንደ ሁሉም ተራ ዜጋ common sense ላይ ተመስርቼ ነው። በህገ ልቦና የተገነዘብኩት ነገር በአጭሩ ልንገርህ። ባገራችን በርካታ ኮንስትራክሽኖች ሲከናወኑና በጣም ጥቂት ሰዎች ከምንም በመነሳት በእጭር ጊዜ ውስጥ ባልታወቀ ምከንያት ሚሊዬነር ሲሆኑ ማየት የተለመደ ነው። ሰፊው ህዝብ ብለን የምንጠራው በሚሊዮኖች የሚቆጠረው ህዝብ ግን እጅግ በከፋ ድህነት ሲሰቃይና ድህነቱ ከጊዜ ወደ
    ጊዜ እየከፋ ሲሄድ እንዲሁም በችጋር ምክንያት ብዙ ቤተሰቦች ሲበተኑ ታያለህ። የኑሮ ውድነቱ እጅግ አሰቃቂ ነው ቢባል ማጋነን አይደለም። እጅግ ሃብታሞችና በሚዘገንን ድህነት ወስጥ የሚኖሩ ዜጎች በአንድ ባንዴራ ስር መፈጠራቸው ኢኮኖሚ የማደግ ምልክት ከሆነ ፍርዱ ለአንባቢያን እተወዋለሁ። ከጥቂቱ እድለኞች በስተቀር ሁሉም ዜጎች ማለት ትችላለህ እያንዳንዷን ቀን በሰቀቀንና በፍርሃት የሚኖሩበት የኢኮኖሚ መዋቅር መዘርጋት የኢኮኖሚ ማደግ ነው ለማለት ያስቸግራል። ያገሪቱ ወጣት ባብዛኛው በስራ አጥነትና በአደንዛዥ ዕፅ የዘፈቀ ኢኮኖሚ የመልካም ኢኮኖሚ መገለጫ ነው ማለት እርስ በርሱ የሚጣረስ አስተሳሰብ ለማስታረቅ መሞከር ነው። ከዚህ ሌላ ምንም ያልነበረው ካዝና ውስጥ መቶ ብርም ከታየ ቁጥሩ ለውጥ ነውና በዚህ ዓይነት ስሌት ከሆነ ምናልባት መንግስት የራሱን ሰዎች ደስ ለማሰኘት ያዘጋጀው መላ ሊሆን ይችላል።
    ል/ህ፡ ለህዝቡ ኑሮ አለመሻሻል ተጠያቂው ማን ነው ብለው ያምናሉ?
    ወ/ሮ መንበረ፡ አሁንሞ እንደ ባለሙያ ሳይሆን እንደዜግነቴ የሚሰማኝን እነግርሃለሁ። መጀመሪያ አንዲት ሃገር እንድታድግ መልካም አስተዳደር ያስፈልጋታል። ለህዝብ የሚጠራ መንግስትና ህዘቡ የሚቆጣጠረውና የሚያርመው ቢሮክራሲ ሳይኖር እንዴት አድርጎ ነው የኢኮኖሚ ዕድገትና የኑሮ መሻሻል የሚመጣው? በዚህ ላይ ሙስናው ጣራ የነካ ነው። ማንም ሰው ወደ መንግስት መስሪያ ቤት ሄዶ ካለጉቦና መጉላላት መብቱ የሆነውን ነገር ማስፈፀም አይቸልም። ቀደም ሲል እንደነገርኩህ በጣም በአጭር ጊዜ ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር እየተመሳጠሩ ሚሊዬነር የሚሆኑ ሰዎች ከየት አመጣችሁት? ይሄ ሁሉ ሃብት ታክስ ከፍላችሁ ካገኛችሁት ገቢ የተገኘ ነው? ብሎ የሚጠይቃቸው አካል የለም። በአንፃሩ ደግሞ በጣም አነስተኛ ቢዝነስ ያላቸው ሰዎች ሊከፍሉም ሆነ ሊያስቡት የማይችሉትን ግብር በማምጣት ከስራ ውጭ ይሆናሉ፡ አቤት የሚሉበት ቦታም የለም። መንግስት የህዝብ አስተዳደር ስራን ትቶ አእራሱ በፓርቲዎቹ በኩል የሸቀጣሸቀጥ ንግድ ውስጥ በገባበት ኢኮኖሚ ፍትሃዊ ወድድር የለም። ፍትሃዊ ውድደር በሌለበት ሲስተም ደግሞ ኢኮኖሚ ሊያድግ አይችልም።
    ል/ህ፡ በርስዎ ግምት አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ከስልጣኑ በቀላሉ ይለቃል ብለው ያምናሉ?
    ወ/ሮ መንበረ፡ ካለኝ ልምድ የማምንበት አንድ ጉዳይ ካለ ከእግዚአብሄር መንግስት በስተቀር የማይወድቅ መንግስትና ስርወ መንግስት በዚህ ምድር ላይ ታይቶ አይታወቅም። ይህ መንግስት ከአፄ ሃይለስላሴ ወይም ከደርግ የበለጠ ተቀባይነትና ድጋፍ የለውም። እነርሱ እንኳ ወድቀዋል። የሚወድቁ የማይመስሉህ እንደ ሳዳም ሁሴን፣ ጋዳፊና ሙባረክ ያሉት መንግስታትና መሪዎች እንኳ ቀናቸው ሲደርስ ወድቀዋል። ይህ የጊዜ ጉዳይ ነው። ጊዜ የማያሳየን ተዓምር የለም።
    ል/ህ፡ ውድ አንባቢያን ቀሪውን ቃለ ምልልስ በክፍል ፪ ዝግጅታችን ይዘን እንቀርባለን። ቸር እንሰንብት።

Comments are closed.

Share