ቃለ ምልልስ (ነቢዩ ሲራክ)

በሊባኖስ ከ4ኛ ፎቅ ከወደቀችው ከእህት ብርቱካን ጋር

    አንዲት እህት ከአራተኛ ፎቅ የመውደቋ መረጃ በሊባኖስ መገናኛ ብዙሃን ሲሰራጭ ከነሰቅጣጭ  ተንቀሳቃሽ ምስሉ ነበር ፣ ኢትዮጵያዊቷ እህት ብርቱካን ነበረች  ! ለኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ሃገር ቤት የገባችው በአልማዝ ጉዳት ስንቆሰዝምና ” የረጅ የደጋፊ ያለህ !” በማለት እርዳታ ስናሰባስን ከወደ ሊባኖስ ቤሩት በእህት ብርቱካን ላይ ሆኖ አይተነው የሰቀጠጠን ፣ ሰምተነው ያመመን አደጋ ልባችን ሰበረው: (

    ብዙም ሳይቆይ በብርቱካን ዙሪያ አወዛጋቢ ሪፖርቶች መቅረብ ጀመሩ ፣ እድሜ ለሥነ ቴክኖሎጅ ወሎ አድሮ ነገሩ እየጠራ መጣ  ! በሊባኖስ ከሚገኙ ለሰብዕና ባደሩ ቅን ወዳጆቸ ትብበር የብርቱካንን ጉዳይ በቅረብ በመከታየል ብርቱካን ያለችበት ሁኔታ በአንደበቷ እንድታስረዳን ያደረግነው ጥረት ተሳክቷል ! ከብርቱካን በተጨማሪ ጉዳዩ ሚመለከታቸውን ሃላፊዎችና ሃኪሞች በጉዳቷ ዙሪያ አነጋግሬያቸውም ነበር ።  የህክምና ባለሙያዎችና በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ሃላፊዎች  እንዳሉት ከሆነ ብርቱካን  የደረሰባት ጉዳት ለከፋ አደጋ ስላልዳረጋት በቀጣይ ቀናት ከሀኪም ቤት በመውጣትና በተዘጋጀላት ማረፊያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን በፍርድ ቤት እንደምትከታተል ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች  ያስረዳሉ ።

ከዚህ በማስከተል በትናንት ሃሙስ ህዳር 3 ቀን 2007 ከቀትር በኋላና አመበሻሹ ላይ እኔ ከሳወዲ ጅዳ ብርቱካንን ከሊባኖስ ቤሩት ሆስፒታል በመሆን በስልክ ያደረግነውን ቃለ ምልልስ ትከታተሉት ዘንድ ግብዣየ ነው  !
ቸር ያሰማን

ህዳር 4 ቀን 2007 ዓም

http://youtu.be/GZhzsDEh5ho

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሕወሐት በአዜብ ጉዳይ ተወጥሯል - (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

1 Comment

  1. እግዝያበሀር እንዋን አዳነስህ ዋናው ያ ነው ገኢን ይሀ ድመሸ የስዋ ነው ? ሚከንያቶም እንደት ካልምኪንያት ተወድካለችህ ደገሞ ትወርወራ ነው ይውደከችሀው ላልመናገር ያስፈራርራት ሰው አለ ባይ ነነ ቭኢእዶ በትኪከል ያሳያል ሰው እንድወርወራት ደገሞ እንደት ነው ክ 4 ተጃ ፎከ ትወርወራ ማተስበረው እንባሰ የመትሎኦት ደገሞ እጋ እትይፕያኖችህ እምባሰ ይምባል የልንም መናልባት ል ትቭ እንድምጅከረብ ሰልታወክ ትበሎ ኮዳስ ልማስወድድድ ሰባል እርዳታ ክተደርግላት አልኪም ንገር ገን ከ ክደም ማንጃዋም እኢትዮፕያወት እርዳታ በተስሃ ማኒም ሰው ዞር በሎ ይተይኪ የሊም እርሳችሀን በይ ኮስህስሃ ቦታ ስወርወእር ይዝገነት ገደታ ስባል የትንከሳክሰ የኢልም እንደን በርቶካን ይምሰአሰሎ በታም ክ ሚልሊን በላይ ናችሀው ያልተናኮ ጊን መን የደርጋል

    ልማንጋወም እግዝያበር ልሃገርዋ ያበካት

Comments are closed.

Share