May 21, 2013
3 mins read

! …. ባህር ዳር አነባች…….!

Abrham Desta

ምነው ይህን ሁሉ???

“ሰካራም” የተባለው የፌደራል ፖሊስ መኮንን አስራ አራት ልጆችሽን ፈጀ። ይህን ሁሉ ግድያ ሲፈፅም (መንግስት ባለበት ሀገር) ሊያስቁመው የቻለ (ወይ የሞከረ) ሃይል እንዳልነበረ ስንሰማ ግራ ገባን። የገዳዩ ማንነት ለተወሰነ ግዜ ሲደበቅብን (የወንጀለኛ ማንነት መደበቅ አስፈላጊ ስላልሆነ) ለተለያዩ መላምቶች ተጋበዝን። (ስሙ ስለተደበቀ ይመስለኛል) ጉዳዩ ከብሄርና ከፖለቲካ ተቀላቀለብን። ‘መንግስት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ስላለበት ተጎጂዎቹን ለማዳን መንግስታዊ ሓላፊነቱን አልተወጣም’ ብለን አለፍነው። መንግስት ታጣቂዎችን (ፌደራል ፖሊሶች ጨምሮ) የህዝብ ደህንነት እንዲጠብቁና በህዝብ ጉዳት እንዳያደርሱ የመቆጣጠር ሓላፊነት አለበት።

ሓዘናችን ሳንረሳ የጣና ሃይቅ አደጋ ደረሰ። የአደጋው መንስኤ በትክክል እስካልታወቀ ድረስ ‘የተፈጥሮ አደጋ (ከቁጥጥራችን ውጭ) ነው’ ብለን ለተጎጂዎቹ አፅናንተን ሳንጨረስ ሌላ የእሳት አደጋ መድረሱ እየሰማን ነው። (በጣና ሃይቅ በደረሰው አደጋ የሞቱ ሰዎች አምስት መድረሱ ተነግሮናል)።

በጅንኣድ (በባህርዳር) ያጋጠመ የእሳት አደጋ እስካሁን በቁጥጥር ስር እንዳልዋለና ወደ ሌሎች አከባቢዎች እንዳይዛመት ተሰግቷል። የእሳት አደጋው መንስኤ እስካሁን ካልታወቀ የራሳችን መላምት ብንሰጥ አይከፋም። የአደጋው ምክንያት ይሆናል ብዬ የምገምተው (“ጥያቄ አለኝ ጓዶች” በሚል የፌስቡክ ስም የሚጠቀመው ወዳጄ እንዳስቀመጠው) ሙስና ነው። የድርጅቱ ሰራተኞች ብዙ የመንግስት ሃብት በሙስና ዘርፈው ይሆናል (ወይ እንበል) የድርጅቱ ንብረት ኦዲት ተደርጎ የፈፀሙት ሙስና እንዳይታወቅ ሰነዶችን የሚጠፉበት መንገድ ማመቻቸት ግድ ይላል። ለዚህኛው ጥሩ መፍትሔ ደግሞ ድርጅቱ በእሳት ማቃጠል ነው። (መላምት መሆኑ ነው።)

እንዲህ ዓይነት ሙስናን ለመሸፋፈን የሚወሰድ እርምጃ በትግራይ ክልል በተደጋጋሚ ሲሰራበት ቆይቷል። በትግራይ ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች (ሙስናን ለመሸፈን ሲባል) በእሳት ተቃጥለዋል። ሁለት ኪሳራ መሆኑ ነው (1) የመንግስት ገንዘብ በሙስና ይወስዳሉ፣ (2) ይህን ሳያንስ የበሉበት ተቋም በእሳት ያወድማሉ።

It is so!!!

2 Comments

  1. የቀረቡት መላምቶች ገናለገና በይሆናል ሰውን የሚወነጅሉ ስለሆኑ ተቀባይነት የላቸውም። ለዚያውም እኮ የጀልባውም ሆነ የእሳቱ አደጋዎች ከኢሳት ውጪ በገለልተኛ አካላት አልተረጋገጡም።

  2. የተቆሉበት የባህር ዳር “የደም ዳር” ሆነች በለው!”ሐዘን ሐዘንን ይወልዳል!” አሉ በዚያን ሰሞን ደረት ተደቃ፣ ሽላሎው ረግዶው፣ ፉከራው ለመሆኑ በእግዝሐብሔሩ ላይ ነበርን?፣ንፍሮ ተወቃ፣፷ሺህ የድሃ ልጅ አፉን ከፍቶ ቂጡን ከድንጋይ የሚያለፋበት እስታዲየም ተመረቀ፣ብሄር ብሄረሰቦች ከበሮ ተደለቀ፣ አድባሩ አውጋሩ ደነገጠ፣ዕድገት በዝቶ ፈሠሠ፣ግን የጎጃሜው ልጅ ዛሬም በባዶ እግሩ ይሄዳል በአዲስ አበባ ከተማ ሎተሪ አዟሪ፣የቀን ሠራተኛ፣ዘበኛ፣ሸቃይ፣ ሆኗል ።የሽማግሌ ቤተሰቦቹ መሬት ከጀርባው ይቸበቸባል። ጎንደር መሬት ይነጠቃል፣ ይቆረሳል፤ ውሃ፣ትምህርት የለም፣መብራትና ስልክ የለም፣ ታዲያ አነኝሁ ታማኝ አገልጋዮች ብቻ በሆቴል ተምነሽንሸዋል። ወያኔ የፈጠራቸው መስለው ለአሳዳሪዎቻቸው ይሰግዳሉ፣የባሕር ዳር በአቶ መለስ የተፈጠረች አድርገው ይሞላፈጣሉ።ወያኔን መርቶ በማስገባት ባለባንዲራ ሆነዋል።በደርግም ፳፪ ከፍተኛ አመራር ከዚያው ሠፈር ነበሩ። ያም ማለት ለዚህ ትውልድ መተራመስ፣ ለሀገር ክህደት፣ለወደብ ማጣት፣ለሠንደቅ ዓላማ ውድቀት፣ለታሪክ ጥፋትና፣ለብሔር ጥላቻና ቅራኔ መፈናቀል ከፍተኛውን ድርሻ የተጫወተው ብአዴን (አልማ) የኢፈርት መንትያ፣ ማጭበርበሪያ የተፈጠረው በግፍና በድሃ ደም ነው። ለድሃው ዜጋ እናዝናለን! እንዳይማር! እንዳይጠይቅ! እንዳይናገር! ላፈኑት ሆድአደርና አድር ባዮች ዩቀም ስቅላት ያሻቸዋል። ለጠፋው ንብረት፣ለሞቱት ዜጎች፣ ለትውልዱ ብክነት ጌታ አፅናኝና አበረታቻቸው ይሁን ልበ ሙሉ ሀገር ወዳድ ደመላሽ ይወለድ በለው! አሜን

Comments are closed.

3461
Previous Story

ባህርዳር ከተማ የጅንአድ እየተቃጠለ ነው

ayat real estate
Next Story

የአያት አክሲዮን ማህበርና የስራ አመራሮቹ ላይ በእስርና ከፍተኛ በገንዘብ ተቀጡ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop