May 21, 2013
3 mins read

! …. ባህር ዳር አነባች…….!

ምነው ይህን ሁሉ???

“ሰካራም” የተባለው የፌደራል ፖሊስ መኮንን አስራ አራት ልጆችሽን ፈጀ። ይህን ሁሉ ግድያ ሲፈፅም (መንግስት ባለበት ሀገር) ሊያስቁመው የቻለ (ወይ የሞከረ) ሃይል እንዳልነበረ ስንሰማ ግራ ገባን። የገዳዩ ማንነት ለተወሰነ ግዜ ሲደበቅብን (የወንጀለኛ ማንነት መደበቅ አስፈላጊ ስላልሆነ) ለተለያዩ መላምቶች ተጋበዝን። (ስሙ ስለተደበቀ ይመስለኛል) ጉዳዩ ከብሄርና ከፖለቲካ ተቀላቀለብን። ‘መንግስት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ስላለበት ተጎጂዎቹን ለማዳን መንግስታዊ ሓላፊነቱን አልተወጣም’ ብለን አለፍነው። መንግስት ታጣቂዎችን (ፌደራል ፖሊሶች ጨምሮ) የህዝብ ደህንነት እንዲጠብቁና በህዝብ ጉዳት እንዳያደርሱ የመቆጣጠር ሓላፊነት አለበት።

ሓዘናችን ሳንረሳ የጣና ሃይቅ አደጋ ደረሰ። የአደጋው መንስኤ በትክክል እስካልታወቀ ድረስ ‘የተፈጥሮ አደጋ (ከቁጥጥራችን ውጭ) ነው’ ብለን ለተጎጂዎቹ አፅናንተን ሳንጨረስ ሌላ የእሳት አደጋ መድረሱ እየሰማን ነው። (በጣና ሃይቅ በደረሰው አደጋ የሞቱ ሰዎች አምስት መድረሱ ተነግሮናል)።

በጅንኣድ (በባህርዳር) ያጋጠመ የእሳት አደጋ እስካሁን በቁጥጥር ስር እንዳልዋለና ወደ ሌሎች አከባቢዎች እንዳይዛመት ተሰግቷል። የእሳት አደጋው መንስኤ እስካሁን ካልታወቀ የራሳችን መላምት ብንሰጥ አይከፋም። የአደጋው ምክንያት ይሆናል ብዬ የምገምተው (“ጥያቄ አለኝ ጓዶች” በሚል የፌስቡክ ስም የሚጠቀመው ወዳጄ እንዳስቀመጠው) ሙስና ነው። የድርጅቱ ሰራተኞች ብዙ የመንግስት ሃብት በሙስና ዘርፈው ይሆናል (ወይ እንበል) የድርጅቱ ንብረት ኦዲት ተደርጎ የፈፀሙት ሙስና እንዳይታወቅ ሰነዶችን የሚጠፉበት መንገድ ማመቻቸት ግድ ይላል። ለዚህኛው ጥሩ መፍትሔ ደግሞ ድርጅቱ በእሳት ማቃጠል ነው። (መላምት መሆኑ ነው።)

እንዲህ ዓይነት ሙስናን ለመሸፋፈን የሚወሰድ እርምጃ በትግራይ ክልል በተደጋጋሚ ሲሰራበት ቆይቷል። በትግራይ ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች (ሙስናን ለመሸፈን ሲባል) በእሳት ተቃጥለዋል። ሁለት ኪሳራ መሆኑ ነው (1) የመንግስት ገንዘብ በሙስና ይወስዳሉ፣ (2) ይህን ሳያንስ የበሉበት ተቋም በእሳት ያወድማሉ።

It is so!!!

2 Comments

  1. የቀረቡት መላምቶች ገናለገና በይሆናል ሰውን የሚወነጅሉ ስለሆኑ ተቀባይነት የላቸውም። ለዚያውም እኮ የጀልባውም ሆነ የእሳቱ አደጋዎች ከኢሳት ውጪ በገለልተኛ አካላት አልተረጋገጡም።

  2. የተቆሉበት የባህር ዳር “የደም ዳር” ሆነች በለው!”ሐዘን ሐዘንን ይወልዳል!” አሉ በዚያን ሰሞን ደረት ተደቃ፣ ሽላሎው ረግዶው፣ ፉከራው ለመሆኑ በእግዝሐብሔሩ ላይ ነበርን?፣ንፍሮ ተወቃ፣፷ሺህ የድሃ ልጅ አፉን ከፍቶ ቂጡን ከድንጋይ የሚያለፋበት እስታዲየም ተመረቀ፣ብሄር ብሄረሰቦች ከበሮ ተደለቀ፣ አድባሩ አውጋሩ ደነገጠ፣ዕድገት በዝቶ ፈሠሠ፣ግን የጎጃሜው ልጅ ዛሬም በባዶ እግሩ ይሄዳል በአዲስ አበባ ከተማ ሎተሪ አዟሪ፣የቀን ሠራተኛ፣ዘበኛ፣ሸቃይ፣ ሆኗል ።የሽማግሌ ቤተሰቦቹ መሬት ከጀርባው ይቸበቸባል። ጎንደር መሬት ይነጠቃል፣ ይቆረሳል፤ ውሃ፣ትምህርት የለም፣መብራትና ስልክ የለም፣ ታዲያ አነኝሁ ታማኝ አገልጋዮች ብቻ በሆቴል ተምነሽንሸዋል። ወያኔ የፈጠራቸው መስለው ለአሳዳሪዎቻቸው ይሰግዳሉ፣የባሕር ዳር በአቶ መለስ የተፈጠረች አድርገው ይሞላፈጣሉ።ወያኔን መርቶ በማስገባት ባለባንዲራ ሆነዋል።በደርግም ፳፪ ከፍተኛ አመራር ከዚያው ሠፈር ነበሩ። ያም ማለት ለዚህ ትውልድ መተራመስ፣ ለሀገር ክህደት፣ለወደብ ማጣት፣ለሠንደቅ ዓላማ ውድቀት፣ለታሪክ ጥፋትና፣ለብሔር ጥላቻና ቅራኔ መፈናቀል ከፍተኛውን ድርሻ የተጫወተው ብአዴን (አልማ) የኢፈርት መንትያ፣ ማጭበርበሪያ የተፈጠረው በግፍና በድሃ ደም ነው። ለድሃው ዜጋ እናዝናለን! እንዳይማር! እንዳይጠይቅ! እንዳይናገር! ላፈኑት ሆድአደርና አድር ባዮች ዩቀም ስቅላት ያሻቸዋል። ለጠፋው ንብረት፣ለሞቱት ዜጎች፣ ለትውልዱ ብክነት ጌታ አፅናኝና አበረታቻቸው ይሁን ልበ ሙሉ ሀገር ወዳድ ደመላሽ ይወለድ በለው! አሜን

Comments are closed.

3461
Previous Story

ባህርዳር ከተማ የጅንአድ እየተቃጠለ ነው

ayat real estate
Next Story

የአያት አክሲዮን ማህበርና የስራ አመራሮቹ ላይ በእስርና ከፍተኛ በገንዘብ ተቀጡ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop