July 1, 2014
6 mins read

“የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም” – ግንቦት 7 (መግለጫ በአንዳርጋቸው ዙሪያ)

ከግንቦት 7 አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ

ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም

የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።

ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።

መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።

በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።

በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

5 Comments

  1. እናንተም ባለስልጣኖችን ነጥሎ የመምታት ስራ ብትጀምሩ አሪፍ ነው ለእያንዳንዱ የወያኔ እርምጃ በቂ የሆነ የበቀል እርምጃ መውሰድ መቻል አለባችሁ።

  2. ተባለእንዴ ዋጋ መከክፈል ማለትም መስዋዕት መክፈል እንዲህ ቀላል ነው? ለነገሩ እቺ ኣጋጣሚ ጥሩ የገንዘብ ማሰባሰብያ ኣጋጣሚ ነች ኣቶ ኣንዳርጋቸውም ብሩ ከተሰበሰበ በሃላ ይፈታሉ ወየልህ የዋህና በቀላሉ የመምትታለል ወገኔ። እቺን ሙድ ለማህሙድ ኣለ ኣንዱ ወዳጄ የመነኖች ደሞ ያለምንም ጥፋት የራሳቸው ያልሆነ ዜጋ ማሰር የጀመሩት መቼ ነው?

  3. ይመስለኛል ግምቦት ሰባቶች በ”መሪያቸው” መለቀቅ ተስፋ የቆረጡ ይመስለኛል:: ትግል በማስፈራራት ለድል አይበቃም:: ስለዚህ በማቅራራትና “ዋጋ ያስከፍላል” ምናምን እያላችሁ ከምታስቁን እስቲ ደግሞ ሌላ ነገር ማለቴ ካሁን በፊት በወያኔም ቢሆን ያልተሞከረ አዲስ “የትግል ስልት” ነገር ይዛችሁ ብቅ በሉ:: ዚሃር ያጥናችሁ

  4. ነገ ከስሩ ተነቅሎ ለሚጠፋው የወንበዴ ሽፍታ እና አገር አስገንጣይ የሆነው የሌባ ስብስብ ወያኔ/ህወሀት ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍለው ከባድ መከራ ከፊቱ ተደቅኗል፡፡ በግንቦት 7 አመራር በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሚፈጸመው እርምጃ ኮብራዎችን የግንቦት 7 ታጋዮች የበለጠ እንዲናደፉ የሚያደርግ ስለሆነ ወሮበላ ሌባ የሆናችሁ የወያኔ ካድሬዎች አስቡበት! አስቡበት!

    የመንም የኢትዮጵያ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት ከሆነው ስርዓት ጋር መተባበርሽን አቁሚ፡፡ ወያኔ ህወሀት/ኢህአዴግ የየመንን ህዝብ ሲያጨፈጭፍ የነበረውን እና የየመን ህዝብ ጠላት የሆነውን አሊ አብዱላህ ሳላህ በኢትዮጵያ ደብቆ የሚገኝ በየመን ህዝብ ላይ ወንጀል ሲፈጽም የነበረ አገዛዝ ስለሆነ የመኖች አስቡበት!

Comments are closed.

Previous Story

Sport: የፊርማ – ከገነነ መኩሪያ (ሊብሮ)

Next Story

የግንቦት ሰባት የአመራር አባል የሆኑት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ደህንነት ሽንጎን ያሳሰበዋል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop