የከተማውም የጫካውም የአብይ አህመድ ገዳይ ቡድን አቅሙ ሩጠው ማምለጥ፣ታግለው መጣል የማይችሉ አዛውንቶች ላይ ነው።
ነፍስ ይማር አባታችን!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመካነ ቅዱሳን አርቱ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያንን በማገልገል ላይ የሚገኙ ፤ ታላቁ የጸሎት አባት አባ ተክለ አብ እና ቀሲስ መሠረት ፤ መስከረም 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡30 አካባቢ ፤ በታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ተደብድበውየተገደሉ ሲሆን ፤ መርጌታ ፍሰሐ እና መርጌታ ተቅዋም የተባሉ አገልጋዮችን ታፍነው ተወስደዋል፡፡
ቦታው በርካታ ጸበልተኛ የሚገኝበት ነው። በቤተ ክርስቲያንና አገልጋዮች ላይ ያነጣጠረው ጥቃት ፤ በታላቋ የጸበል ቦታ በመካነ ቅዱሳን አርቱ ቅድስት አርሴማ የተፈጸመው ይኼ አሰቃቂ ድርጊት አስመልክቶ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ፣ የሰማዕታቱ ጸሎተ ፍትሐት እና ስርዓተ ቀብራቸው እየተካሄደ ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ዝምታ ለምን ይሆን ?!
“ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ።
እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይደርሳል።” ማቴ ፳፫: ፴፭ – ፴፮።
ካህኔን ከመቅደሱ ገድለውብኝ እንዴት ዕረፍት ይሰማኛል? እንዴት ዕረፍት ተሰማን?