ጸረ-ሴማዊ ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ፡ የኦሮሙማ አዲስ አሰላለፍ

በግርማ ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)

መግቢያ

ብሄር ተኮር ፌደራሊዝም በሚባል ክፉ የመንግስት ስርዓት ምክንያት ኢትዮጵያ ለከፍተኛ ችግር ተዳርጋ ቆይታለች። እ.ኤ.አ. ከ1990ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ ጥላቻን አንግቦ ለዙፋን የበቃው ቡድን በማርክሲስት ቋንቋ “ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች“ እያለ ከፋፋይ ዘረኝነትን ሲያሰርጽ ቆይቷል። ይህ በስሁት የጥላቻ ትርክት ላይ የተመሰረተ ህዝቡን በዘውግ የመከፋፈል ሂደት በስሪቱ የደቡብ አፍሪካን የአፓርታይድ መንግስት የባንቱስታንን ፖሊሲ የደገመ ነው። ‘የብሔር ማንነት’ በሚል ሽፋን በክልሎችና ብሔረሰቦች መካከል የስልጣን ግብግብ ሲፈጠር ማዕከላዊው መንግሥት እየተንኮታኮተ ስለሚሄድ፡ ቀድሞ የተደራጀው ዘውግ አብላጫ አቅም አግኝቶ ሌሎቹን እርስ በእርስ እያፋጀ እንዲኖር የሚያስችል መርዛማ የከፋፍለህ ግዛ ሥርዓት ነው።

በ1970ዎቹ እና 1980ዎቹ መጨረሻ ደቡብ አፍሪካ ላይ እንደነበረው ሁሉ ይህ የብሄር ፌደራሊዝም ስርዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ቀብሮት የቆየውን ጥላቻ አፈንድቷል። በየአካባቢው በሚገኙ የጥላቻ ፖለቲካ ነጋዴዎች እየተቀሰቀሰ ካለው ተደጋጋሚ የንጹሀን ዜጎች እንግልትና እልቂት በተጨማሪ እስከ አፍንጫ የታጠቁት ሁለቱ ቡድኖች [ኦነግና ትህነግ] የብሔር ፌደራሊዝም መዋቅራዊ ተግዳሮቶችን እንደ ጥቅም በመውሰድ ለራሳቸው ዓላማ በማዋል ላይ ናቸው። በኦነግ እና የ4ኪሎ ምስለኔው የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) አቻ አቋም ተወስዶ በጋራ እየሰሩት ያለው፥ በሴማዊና በኩሽ ተወላጆች የዘር ትርክቶች ላይ የተመሰረተ የሰሜን-እና-ደቡብ ጦርነት ማድረግ ነው። ኦነግ ኦሮሞን በኩሽ ይፈርጅና ታማኝ፣ ታታሪ እና በሚያሳዝን ሁኔታ ተጨቋኝ አድርጎ ያቀርባል። በዚህ ጥርክት መሰረት የኩሻዊው ተጻራሪ አታላይ፣ ጥገኛ እና በዝባዥ የሆነ አማራ የሚባል ነገዱ ሴማዊ የሆነ ህዝብ ተሰርቶለታል። አሰላለፉ አማራውን ለማጥፋት የተሰራ ግልጽ አዋጅ ነው። የናዚ ርዕዮተ ዓለም ከግማሽ ምዕተ አመት በኋላ በሀገራችን ስራ ላይ እንደሆነ መታወቅ አለበት።  አስተሳሰቡም ሆነ መሬት ላይ እየተፈጸመ ያለው ድርጊት በ20ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በሩዋንዳ ሁቱዎችን እና ቱትሲዎችን ለዘር ፍጅት የዳረገው ትርክት ዋና ቅጂ ነው።

ከአንድ ትውልድ በፊት በሩዋንዳ  እንደነበረው፣ ሁሉ መርዛማ ትርክቶች በከፍተኛ ደረጃ የመንግስት ፖሊሲ ውስጥ ሰርገው ገብተዋል። ኦነግ ከስድብ እና የጥላቻ ንግግር ወደ ግልፅ ጠላትነት በማሸጋገር በአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ ‘ሴማዊ ሰፋሪዎች ናቸው’ ብሎ በመነጠል ጦርነት አውጇል። በደቡብ፣ በምስራቅ እንዲሁም በምዕራብ ኢትዮጵያ ባሉ ከተሞች እና አማራ በብዛት የሚኖርባቸው መንደሮች በየዕለቱ ጅምላ ግድያዎች ሲደረጉ፡ ከሁከቱ በስተጀርባ ያለው ትረካ ‘መጥፎውን አረም ማስወገድ’  ማለትም ሴማዊ አማሮችን መግደል ነው።

ኦነግ ግልፅ ማኒፌስቶ አውጥቶ በአማሮች ላይ በሁሉም ዘርፍ ጦርነት ካወጀ ብዙ ቆይቷል።  የአምልኮ ቦታዎችን ማርከስ፣ ቀሳውስትን ማዋረድና በግፍ መግደል፣ በአማርኛ ቋንቋ የሚናገሩትን ማስፈራራትና መደብደብ በገሀድ በየቀኑ የሚከናወን ሽብር ሁኗል።  ባጭሩ ኦነግ እና ገዢው ኦህዴድ ኢትዮጵያን በጦርነት ለማፍረስ እና ለዚች ጥንታዊት ሀገር ህልውና እና ነፃነት ማዕከላዊ ሚና የተጫወቱትን ህዝቦች ለማጥፋት የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥተው እየሰሩ ነው።

የዚህ ጽሁፍ ትኩረት መላውን ምስራቅ አፍሪካን እየናጠ ያለውን በጸረ ሴሜቲዝም ዘረኝነት ላይ ያተኮረውን የኦሮሙማ ርዕዮተ ዓለም አደጋን መመርመር ነው። ሻለቃ ዳዊት (2023) ኢትዮጵያ ውስጥ በዐማሮች ላይ የሚፈፀመውን ዘር ጭፍጨፋ ለመመርመር የተሳተፈ የሕግ ባለሞያዎች ሁሉ እንዳረጋገጠ በአጭሩ አስረድቷል። ኢትዮጵያ ውስጥ የዘር ማፅዳትና የኩሽ ኢምፓየር ለመመሥረት በማሰብ የሴማውያንን ዘር የማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመ ነው። እንደ ኩሽ ሚዲያ እና ኦሮምኛ መዛግብት ሀተታ፡ ሴማዊ (በተለይ አማራዎችና ትግራውያን) በሚገርም የታሪክ ሸውራራ አተያይ የኩሽ ተወላጆችን ቅኝ የገዙ ተደርገው ይወሰዳሉ። ይህ የታሪክ አተያይ ባለፉት 4 ዓመታት የተከሰተውን የዘር ማጥፋት፣ በንጹሀን አማራ ዜጎች ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ወንጀሎች እና የጦር ወንጀሎች፥ የሦስት ሚሊዮን ሕዝብ ሞትና 4 ሚሊዮን አማሮች መፈናቀል አስከትሏል። አለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲነቃና ይህን እብደት እንዲያስቆም ስንት መሞቶ ስንትስ መፈናቀል አለበት? (1)

በዚህ ጽሑፍ የሚዳሰሰው አሳሳቢ ጉዳይ ከቀደመው አፓርታይዳዊ አገዛዝ ፖሊሲ በባሰ ሁኔታ እየቀጠለ ያለው የብሄር አፓርታይድ ስርዓት ውስጥ የኦሮሞ ባለስልጣናት ያሳዩት የመስፋፋት ስግብግብነት ነው። ይህ መዋቅራዊ ይዘት ያለው የኦሮሞ ብሔርተኞች [Oromummaa] ዋና አጀንዳ ነው። ኦሮሙማ [Oromummaa] ውስብስብ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፕሮጀክት ነው። እንደ ሀገራዊ ፕሮጄክት እና የኦሮሞ ብሄራዊ ንቅናቄ ማዕከላዊ አስተሳሰብ፡ ኦሮሞዎች ባህላዊ እሴትና ማንነታቸውን እንዲላበሱ ያስችላቸዋል፣ “የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት” እያሉ የሚጠሩትን ትርክት እንዲገመግሙ፣ የጋራ ቅሬታቸውን እንዲያሰሙ፣ የተለያዩ የባህል ሀብቶችን እንዲያንቀሳቅሱ፣ በኦሮሞነት እንዲሰባሰቡ፣ የግልና የጋራ ግንኙነቶችን ኦሮሞን ባማከለ የፖለቲካ ስልት ለማድረግ እና  ህዝቡን ለነፃነት የሚያጎናጽፉ የጋራ ተግባራትን ለመቀየስ ይረዳል። (2)

በዚህ ረገድ የኦሮሙማ ደቀመዛሙርት ሁነው የሚጽፉና የሚተነትኑ ልሂቃን ‘የኦሮሞ ብሄራዊ ንቅናቄ ሁሉንም ሰው ያሳተፈ እና በዲሞክራሲያዊ መንገድ የሚፈጸም እንደሆነ ቢያትቱም መሬት ላይ የሚታየው እውነት ግን ኢትዮጵያን ማፍረስ አልያም ፍጹም የኦሮሞ የበላይነትን ማረጋገጥ የሚፈልግ፤ ጠብ አጫሪ እና ከኦሮሞ ውጭ የሆነውን ኢትዮጵያዊ ከማንኛውም ተሳትፎና ተጠቃሚነት የማግለል ሂደት ነው። ከምንጊዜውም በበለጠ ስልጣንን አላግባብ መጠቀም እና አረመኔአዊ አፈናዎች ተስፋፍተዋል። በዚህ አስከፊ እውነታ ውስጥ በኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም በአማራው ህዝብ ላይ የተዘረጋው ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ባህላዊ ገጽታን እያወሳሰበ ያለው አስፈሪ የጥላቻ ፖለቲካ አዙሪት ነው። ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ የዚህንን ጽንፈኛ ቡድን ቀጠናዊ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊረዳውና የአፍሪካ ቀንድ መናጋት ሊፈጥረው የሚችለውን ቀጠናዊ ቀውስ ሊገነዘበው ይገባል።

ሌላው የዚህ ጽሑፍ የትኩረት መስመር በኦሮሙማ እና በፋሺዝም/ሂትለሪዝም መካከል ያለውን አስደናቂ መመሳሰል ማሳየት ነው። የፋሺስት ፓርቲዎች እና ንቅናቄዎች አንዳቸው ከሌላው በእጅጉ ቢለያዩም በሚያሳዩት ጽንፈኛ ወታደራዊ ብሔርተኝነት፣ ለምርጫ ዲሞክራሲ ባላቸው ንቀት እና የፖለቲካ እና የባህል ሊበራሊዝም ላይ በሚይዙት ግርድፍ አቋም፣ እንዲሁም በሚያራምዱት ማህበራዊ ተዋረድ እና የልሂቃን አገዛዝ ላይ በሚኖራቸው ጥብቅ እምነት ከፍተኛ የመመሳሰል ባህሪያት አሏቸው። በተጨማሪም ለቡድኑ ጥቅም ሲባል የግለሰቦች ፍላጎቶች የሚደፈጠጡበት ‘ሕዝባዊ ማህበራት’ (ጀርመንኛ፡ “a Volksgemeinschaft”) (3) ተመስርተዋል። በዚህ መልኩ ብሔርተኝነቱ “እኛ” እና “እነሱ” በሚል ክፍፍል ስለሚደራጅ ዋልታረገጥ ጽንፈኝነትና ሌላውን ጠልነት ያዳብራሉ። ሙሉውን ማለት በሚቻል ደረጃ ለጥላቻ የሚጠቀሙበት ትርክት በአፈ ታሪክ ላይ የተመሰረተ እና  በወታደራዊ አቅም፥ በፖለቲካ እንዲሁም በባህል ላይ የበላይነት ያለው ኢምፓየር የመፍጠር ራዕይ አላቸው። (4)

ይህንን አስተሳሰብና እምነት ተከትሎ የሚመጣው ታዲያ የታለመውን የአንድ ብሔር የበላይነት የሰፈነባት ሀገር የመፍጠሩን ሂደት  የሚያደናቅፍ ማንኛውንም ነገር በኃይል መወገድ አለበት የሚለው ሀሳብ ነው። እንዲያውም በፋሽስቶች ታሪክ ለዚህ አፈጻጸም ሲባል የሚወሰድ አሰቃቂ እርምጃ እና ጭፍጨፋ ለህብረተሰቡ ጠቃሚ ተደርጎ ይታይ ነበር። ኦሮሞዎች ይህንን ጉዳይ በትክክል መመዘን ያለባቸው ለኦሮሞዎች የረጅም ጊዜ ጥቅም የትኛው እንደሆነ ነው። እዚህ ላይ በወፍ በረር ብቻ የማነሳቸው ሁለት ጉዳዮች አሉ። የመጀመሪያው የኦሮሞ ጽንፈኞች ገዳ ስርአትን “የኦሮሞ ወግና ባህል እምብርት፤ የኦሮሙማ መሰረት ማድረግ” (5) ከሚሉት በዘለለ የመጨረሻው ግብ እስልምናን እና ኦርቶዶክስ ክርስትናን በማጥፋት(6)  የኦሮሞ ሀገር በቀል እምነትን ስርአታዊ የማድረግ ፍላጎት አለ። ኢሬቻን እና ዋቄፋናን የኦሮሞን ብሔራዊ ማንነት ወደተጠናከረ አንድነት ይወስዳል (7) ተብሎ መታሰቡ ስህተት። ይህ ከባህል አገላለጽ ወደ ፖለቲካ እና ሃይማኖት ማጥፋት መቀየሩ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል። ምክንያቱም ዋቄፈና ሁለቱን ዋና ዋና ሃይማኖቶች እስላም እና ክርስትናን እንዲተካ ነው የታለመው።

ሁለተኛው ጉዳይ የትግራይ ተወላጆች እንደ አማራው ሁሉ የሴማዊ ሰዎች በመሆናቸው በሀገሪቱ ውስጥ የፀረ-ሴማዊ ጥቃት ሰለባ ስለመሆናቸው ነው።  የትግራይ ተወላጆች በዘር ልዩነት እና በጥላቻ መከፋፈል ላይ የተመሰረተውን የአገዛዝ ስርዓት ያመጡትና በመጨረሻ ግን እራሳቸውንም ሰለባ እንደሚያደርግ አይዘነጋም። ሆኖም ግን በትግራይ ተወላጆች ላይ ፀረ-ሴማዊ ጥቃት አሁን በአማራው ላይ በሚደርስበት ደረጃ ያልተከሰተበት ሁኔታ የፋሽስቱ ኃይል ታክቲክና  ከፋፍሎ የማጥቃት ስትራቴጅ ስለሆነ ዝርዝር ጉዳዮችን በሌላ ጽሑፍ አብራራቸዋለሁ።

 

ኦሮሙማ እና ፋሺዝም

ሮፌሰር ኃይሌ ላሬቦ፣ አቻምየለህ ታምሩ እና ዶ/ር ቤዛ አሰፋን ጨምሮ በርካታ የኢትዮጵያ ምሁራን በአረመኔያዊ የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ላይ የተመሰረተውን የኦሮሞ ብሔርተኝነት እና የኦነጋዊነትን ምንነት አጋልጠዋል። ይህ አረመኔያዊ የባህል ቅርስ በፖርቹጋላዊው የእየሱሳውያን ቄስ ፓኤዝ በ1621 “ጋላዎች ስሕፃናትን፣ ሴት ልጆችን፣ ነፍሰ ጡር ሴቶችንና አሮጊቶችን ሲገድሉ” (8) በሚል ርዕስ የጻፈውም ማስረጃ በሚገባ ተመዝግቧል! (9) በመሰረቱ የጋዳ ስርአት ከፍተኛ ወታደራዊ ሃይል የሚጠቀም እና ሴቶችን ሙሉ በሙሉ ያገለለ፤ ኦሮሞ ያልሆኑ ህዝቦችን በዘግናኝ ጭፍጨፋ ዘር በማጥፋት፡ ከዘር መጥፋቱ ጭፍጨፋ የተረፉትን ደግሞ ጸጥ-ረጭ ብለው በአገልጋይነትና ተገዢነት እንዲኖሩ የሚያደርግ ነው። (10) ይህ ጥንታዊ አረመኔ ተግባር ዛሬ በኦህዴድ [ኦነግ የበላይ በሆነበት] ዘር ጨፍጫፊው የአብይ አህመድ መንግስት — በኩሽቲክ ዲስኩር የሚመራው ጦር— “ስልጣኔን ከነካካችሁ መቶ ሽህ ሰው ከእናንተ ወገን አልቆ ያድራል” የሚል ድፍረት ያለው፤  በቀን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ “ለተጨፈጨፉት ሰዎች ጥላ ለመፍጠር ችግኞችን እተክላለሁ!” የሚባልበትን ስርአት አውርሷል። ስለዚህ የአብይ አህመድ የዘር ማጥፋት አገዛዝ አሁን በስልጣን ላይ ባሉት 200 ሰዎች ዘንድ ያለው ጥልቅ የባህል እምነት ከሆነ እኩል ወይም የበለጠ ኃይል እስካልገጠመው ድረስ መቼም አይቆምም! በዛ ላይ ጉዳቱ ቀድሞም ደርሷልና ወደ ኋላም ማየት አይቻልም! ስለዚህ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ የተባባሰ ተመሳሳይ ነገር እንደሚከሰት ግልጽ ነው። (11)

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ልክ እንደ ጀርመን ብሔራዊ የሶሻሊስት ፓርቲ (ናዚ ፓርቲ) የሶሻሊስት ብሄረሰብ ፋሽስት ቡድን ሆኖ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማደሪያ ክፍሎች ውስጥ በሰኔ 1973 ተመሠረተ። (12) የቡድኑ ተልእኮ ሁለት ነበር፡ የኢትዮጵያን መንግስት [ኢትዮጵያን] ማፈራረስ እና የኦሮሚያ ሪፐብሊክን በኢትዮጵያ ፍርስራሽ ላይ መመስረት። አሁን ጥያቄው የመጨረሻውን ተልእኮ ማሳካት ይችሉ ይሆን፣ የምስራቅ አፍሪካን አዲስ የኦሮሚያ ሪፐብሊክ መውለድ ይችላሉ? እንደ ሸገር ፖስት 6/23/2023 ትንታኔ እስካሁን ካየነው የበለጠ ደም አፋሳሽ ጦርነት እና እልቂት የሚኖረው ቢሆንም እቅዱ ግን ሊሳካ እንደሚችል አመላክቷል። (13) በ1991 በኤርትራ ምስረታ ላይ እንደነበረው ወይም በምስራቅ አውሮፓ እንዳየነው አለም አቀፍ ድጋፍ ላይኖር ይችላል። ድጋፍ አያገኝም ብቻ ሳይሆን የማይቋጭ የጦርነት ምዕራፍ መክፈት እንደሚሆን አመላካች የሆኑ ነገሮች በሂደቱ እየተስተዋሉ ነው።

ለምሳሌ፡ አማሮች ለትግሉ እየተዘጋጁ ነው። በወለጋ ጠቅላይ ግዛት የአማራ ንጹሀን ጅምላ ከተጨፈጨፉ በኋላ የአማራ ታጣቂዎች ከመንግስት ጋር ፍጥጫ ውስጥ ገብተዋል። ለህዝብ ህልውና እና ለሀገር አንድነት መስዋእት እንሆናለን ብለው የተነሱት ፋኖዎች ከድል በስተቀር የሚመልሳቸው ነገር ያለ አይመስልም። የአገዛዙ ተጨፍላቂና ተጨቋኝ ህዳጣን ህዝቦችም በቀላሉ ተስፋ አይቆርጡም።  ከአማሮ፥ ቡርጅ እና ጌዴኦ አካባቢ በርካታ እሮሮ ሲሰማ ቆይቷል። በጋምቤላ ህዝቦች ላይ የክልሉ ህዝብ መሸከም ከሚችለው ቁጥር በላይ ስደተኞችን ከውጭ ሀገር በገፍ በማስገባት በእጅ አዙር እየተፈጸመ ያለው ወረራ የጋምቤላ ክልል ህዝብን የህልውና አደጋ ላይ ጥሏል። ይህን ነባራዊ ሁኔታ እያየ የክልሉ ህዝብ ያለኮሽታ ይጠፋልኛል ተብሎ አይታሰብም። አፈና እና አምባገነንነቱ እየተባባሰ ሲቀጥል ጉራጌዎች እና ሱማሌዎችም መሳሪያ ሊያነሱ ይችላሉ። በአጠቃላይ ሀገሪቱ አርማጌዶን ትሆናለች እንጅ የኦሮሚያ ሪፐብሊክ በቀላሉ የሚመሰረት አይሆንም። ነገር ግን ኦሮሙማ ወረራ ማድረግና በተለያዩ ህዝቦች ላይ ጭፍጨፋ ሳያደርግ እንደማይቀር ገሀድ ነው። በሀገራችን ታሪክም በርካታ አስከፊ ወረራ እና ውድመት ማድረሱ በሳይንሳዊ የታሪክ ሰነዶች ውስጥ ተይዟል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የማልስማማባቸው የዳንኤል ክብረት ሃይማኖታዊ ትንታኔዎች

በ1580ዎቹ እና በ1590ዎቹ የኦሮሞ ህዝብ ወደ ቀድሞ የኢትዮጵያ ግዛቶች ቢዛሞ፣ ዳሞት እና ሸዋ ሲደርሱ ብዙ ሴማዊ የሆኑ የጋፋት ክርስቲያን ማህበረሰቦች በእነዚያ አካ ቢዎች ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ1593 የብሔር ብሔረሰቦች ምሁር እና የዘመኑ የነገስታት ዜና መዋዕል ጸሐፊ በነበሩት አባ ባሕርይ እንደተዘገበው ቢዛሞ፣ ዳሞት እና ሸዋ የተባሉ አካባቢዎች የጋፋትን ባህል በሺህ ለሚቆጠሩ ዓመታት ያቆዩት አካባቢዎች ከፍተኛ ውድመት ደርሶባቸዋል። ህዝባቸውም ከጋላው ጭፍጨፋ ሸሽቶ አጎራባች ወደነበሩት ወደ ጎጃም ግዛቶች  እና በወራሪው ኃይል ተደራሽ በማይሆን የሰሜን ሸዋ ተራራማ አካባቢ እና ሌሎች ቦታዎች ተበታትነው ከአካባቢው ባህሎች ጋር ተደባልቀው ነበር (ባህረይ 1954፡ 121–4፤ ቡአንጋ 2013፡ 352–62፤ ቤኪንግሃም እና ሀንቲንግፎርድ 1954፡ 56)። (14)

የታሪክ ፕሮፌሰሩ ሀብታሙ ተገኝ ‘ጋፋት እና ሌሎች ብዙ ብሄረሰቦች ከኦሮሞ ህዝብ ጋር በኃይል ተዋህደው ቀስ በቀስ ጠፍተዋል’። ፕሮፌሰሩ የቢዛሞ፣ ዳሞት እና ሸዋ እና ሌሎችም የመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ መንግሥት ዋና ዋና ግዛቶችን በኦሮሞዎች መቆጣጠሩ እና የተወላጆች ፈጣን እልቂት የዘር ማጥፋት ወንጀል ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ሲሉ ይከራከራሉ። (15)

የጽንፈኛው ኦሮሞዎች የፋሺስታዊ እና የዘር ማጥፋት ተግባር ከመካከለኛው ዘመን ጀምሮ ነው። በአሁኑ ጊዜ በኦሮሙማ የፖለቲካ አስተሳሰብ እየተመራ ተመሳሳይ ውድት እና የዘር ማጥፋት የጥላቻ ንግግሮችን በመጠቀም ምስራቅ አፍሪካን ለመቆጣጠር ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ነው። (16) ዶ/ር ዮናስ ብሩ (17) ‘ኦሮሙማ በናዚዝም ማህበራዊ ስነ ልቦና ተቃኝቶ በ21ኛው ክ/ዘመን የቀረበ የ16ኛው ክፍለ ዘመን ሞጋሳ ነው’ ይሉታል። ሂትለር በህዝቡ ላይ ቁጣ እና ፍርሃት በመፍጠር፣ መሳሪያም በማስታጠቅ የጥቃት ኢላማ ያደረጋቸውን አካላት በመጨፍጨፍ ረገድ ከፍተኛ ስኬት ነበረው። አይሁዶችን ዋነኛ ጠላቶች አድርገው ነበር ያነጣጠሩት። ኦሮሙማም አማራውን እንዲሁም ክርስቲያኖችን እና እስላሞችን እንደ ኦሮሞ ቀንደኛ ጠላቶች በመጠቀም ተከታዮቻቸውን በቁጣ አስነስተዋል። የኦሮሞ ጭካኔ መነሻው “በ19ኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ አስርተ አመታት የጀመረው የኢትዮጵያ ቅኝ ገዥ ሽብርተኝነት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አሁንም በ21ኛው ክፍለ ዘመን እንደቀጠለ ነው” የሚለው መርዘኛ የፖለቲካ ትርክት እና የናዚ (18) የፖለቲካ ስልት ነው። (19) የኦሮሙማ ሊቃውንት መጽሐፍ ቅዱስን ጭምር ወደ ኦሮሞ ማንነት ለመውሰድ አዲስ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ እንዳሳተሙ ደራሲው ገልጿል። ለምሳሌ መዝሙረ ዳዊት 68:31 “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” ይላል። በአዲሱ የኦሮሙማ ትርጉም ደግሞ- “ኩሽ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” ይላል።

ሂትለር ጥላቻን እና ቁጣን እንደ ማህበራዊ ሃይል ተጠቅሞ የአርያን ዘር አንደኛ ምርጥ ዘር አድርጎ እንደሰበከው ሁሉ አሁን የኦሮሙማ ምሁራንም ልክ እንደዛው እያደረጉ ነው። ሂትለር አስጸያፊ የሰው ልጅ ባህሪ ያላቸው ተከታዮችን መፍጠር እንደቻለ ሁሉ ፕሮፌሰር ጃላታ (20) እና የእሱ እንጉጉ ምሁራኖችም ቅንጣት የሞራል ግድ የሌላቸው አስጸያፊ ሰውበላዎችን ፈጥረዋል። የኦሮሞ ብሔርተኝነትን ለመፍጠር በሂትለር የጅምላ አስተምህሮ እና ቅስቀሳ ሂደት በሚመሩ የጎሳ ምሁራን ይመራል። አሁን ኦሮሙማን ችላ የሚሉ ሰዎችም የናዚን እንቅስቃሴ በምስረታ አመታት ችላ እንዳሉት ሰዎች ናቸው። (21)

ታሪካዊው የኦሮሞ መስፋፋት፥ አጎራባች ብሄረሰቦችን የመውረር እና የመግዛት ፍላጎት ኦሮሙማ በአሁኑ ጊዜ እየመከረ ካለው ጋር ተመሳሳይ ነው። የሚከተሉት ጥቅሶች በ16ኛው ክፍለ ዘመን የነበረውን የግፍ ደረጃ ይገልፃሉ። “የኦሮሞ አረመኔነት በክርስትና መሰረታዊ ጽንሰ ሃሳብ የዶግማ ኃጢአት ነው”። ኢየሱሳውያን የኦሮሞ ወረራ በእግዚአብሔር የተላከ መቅሰፍት እና ቅጣት ነው ብለው ነበር ያመኑት። ማብቂያ የሌለውን የኦሮሞ ወረራ በኢትዮጵያውያን ሃጢያት መብዛት ምክንያት ከእግዚአብሔር የተላከ እንደሆነ ይናገሩ ነበር። ሚስዮናዊው ፔድሮ ፓኤዝ በታዘባቸው ሰባት ዓመታት [1615-22] ውስጥ ‘እግዚአብሔር በዚህ መንግሥት እና በኢትዮጵያውያን ላይ ከፈጸመው ከባድና ቀጣይነት ያለው ቅጣት በቀር ምንም ከባድ ነገር አልተከሰተም’ ሲል ጠቅለል አድርጎ ተናግሯል። “ኢትዮጵያውያን ጥሩ ክርስቲያኖች ከሆኑ፡ ለምንድነው እግዚአብሔር በቱርኮች፣ በመሀዲስቶች፣ በጋሎች፣ በበሽታ፣ በማያባራ ጦርነት የሚያሰቃያቸው?” ይላል። (ፔዝ 2011፡65) (22)

በናዚ እና በኦሮሙማ መካከል ያለው የርዕዮተ-ዓለም እና ሞዱስ ኦፔራንዲ አቻነት በመሠረቱ ከመነሻ እሳቤያቸው መመሳሰል የመነጨ ነው። የሂትለር ርዕዮተ ዓለም የሚያጠነጥነው በእሳቤ ደረጃ “የጀርመን ሕዝብ አንድ ሕያው እስትንፋሳዊ አካል ነው” ብሎ የሚለይና አይሁዳዊውን ደግሞ በዚህ እስትንፋሳዊ አካል ውስጥ ለህመም ወይም ለጥፋት የሚሠራ ኃይል እንደሆነ አድርጎ ይለያል። (23) ሂትለር አይሁዳዊውን አካልን አዳካሚ ኃይል ወይም የመበስበስ ኃይል ብሎ ይጠራዋል። የናዚ ርዕዮተ ዓለም እንደ ህልም ወይም ቅዠት ነበር – ብዙ ሰዎች በተመሳሳይ ጊዜ የገቡበት ቅዠት ነበር። ይህ የጋራ ቅዠት ማህበራዊ እንቅስቃሴን ከመፍጠር አልፎ የታሪክን ቅርጽ መቀየር የቻለ ኃይለኛ ክስተት ነበር። ኦሮሙማም የኢትዮጵያን ሴማዊ ህዝብ የሚለየው እንደዚሁ ነው። ሂትለር በጥልቁ የናዚ ቅዠት ውስጥ ጠልቆ ስለገባ እና ናዚነትም በመላው መንፈስና አካሉ ስለተዋረሰው ቅዠቱን ለጀርመን ህዝብ የማዳረስ አቅም ነበረው። አሁን የኦሮሙማ መሪዎችም የሂትለር ግልባጭ ናቸው። ታሪክ ለመስራት በጥልቅ ቅዠት ውስጥ ናቸው። “የኦሮሞ ንቃተ-ህሊና” መፍጠር ከሂትለር የጀርመን ንቃተ-ህሊና መፍጠር ጋር ተመሳሳይ ነው። ናዚ የአሪያንን ዘር ከሰዎች ሁሉ መጠቅ ያለ ትልቅ ዘር አድርጎ የማቋቋም እና አለምን የመግዛት ተልእኮ ነበረው። በተመሳሳይ መልኩ ኦሮሙማ የጋዳ ስርዓትን እንደ አንድ ገዥ አለምአቀፍ ፕሮጀክት እንዲስፋፋ እና እንዲመለክ ይፈልጋል። (24)

ዶ/ር ዮናስ ሲያብራሩ የኦሮሞ ህዝብ ክርስትና እና እስልምናን እንደ አንድ ባህላቸው አካል አድርገው ይመለከቷቸዋል ብለዋል። በአንጻሩ የኦሮሙማ አስተምህሮ ሁለቱን የአብርሃም ሃይማኖቶች እንደ ኢትዮጵያዊ “ኢምፓየር መስራቾች” አድርጎ ይገልጻቸዋል። አይሁዶች ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ገንብተውታል የተባለው የኢትዮጵያ ኢምፓየር “በኦሮሞ ባህል ላይ ጥቃት በማድረስ ጭካኔ የተሞላበት፣ ግድያ፣ የማሸበር እና የበታችነት ስሜትን [በኦሮሞው ላይ] በማስተዋወቅ” ተከሷል። ፕ/ር ዶናልድ ሌቪን (25) የኢትዮጵያን አንድነት ያስጠበቀው የርዕዮተ ዓለም ሙጫ፡ በተከታታይ በንጉሠ ነገሥቱ ሥር የነበረው “የሰለሞናዊ ርዕዮተ ዓለም” ብለው የሰየሙት እና  በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ጥንታዊ መንግሥትነት ታሪክም በክብረ ነገስት እንደተገለጸው በንጉሥ ሰሎሞን እና በንግሥተ ሳባ መካከል ከነበረው ሕብረት ጋር የተቆራኘ እንደሆነ ያምናል። ይህንን የአስተሳሰብ መስመር ብቻ ሳይሆን አሁን የብዙ ብሔር ብሔረሰቦችን ተዋጽኦና ፍላጎት ያገናዘበ አዲስ አስተሳሰብ እንደሚያስፈልግ ግልጽ ነው። ነገር ግን ከሰለሞናዊው በዘር ሀረግ ከሚወረስ አስተዳደር የተሻለ ስርአት ትሻለች እንጅ ሀገራችን፡ ፈጽሞ በባሰውና ይባስ ብሎም አረመኔያዊ በሆነ እንደ ኦሮሙማ, (26) አይነት ቅዠት እጅ ልትወድቅ አይገባም። ኦሮሙማ በስደት በሚኖሩ የዘውግ ጽንፈኛ የኦሮሞ ምሁራን የተፀነሰው እና የሚያራምደው ርዕዮተ ዓለም በንድፍ እጅግ ከፋፋይ፣ ብሔርተኝነት እና ወገንተኝነትን የሚፈጥር ነው። በመሆኑም መረጋጋትን፣ ሰላምን እና ብልጽግናን ሊያጎለብት ይቅርና ለሀገር ጉዳይ ህዝቡን በአንድነት እንዲቆም የማያደርግ ቅዠት ነው።(27)

ናዚዝም በከፍተኛ ብሔርተኝነት፣ ዘረኝነት እና አምባገነንነት ይታወቅ ነበር። አንዳንድ ምሁራን የበታችነት ስሜት ያለባቸውን ሰዎች አስተሳሰባቸውን በመረዳት ረገድ ያለውን ሚና ቃኝተዋል። የብቃት ማነስ ሲኖር የበታችነት ስሜትን ያስከትላልና ግለሰቦች ባላቸው አቅም የሚፈልጉትን አላማ ማሳካት እንደማይችሉ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በዚህም የተነሳ ስልጣንን በመጠቀም እና ሌሎች ላይ ቁጥጥር ማድረግን እንደማሸነፊያ መንገድ እንዲጠቀሙ ሊገፋፋቸው ይችላል። ለምሳሌ፡ ሂትለር እንደ አርቲስት ተደራራቢ ውድቀቶችን አስተናግዷል። የሀገር መሪ ከሆነ በኋም ቀድሞ ባጋጠሙት ውድቀቶች ምክንያት ያዳበረው ስነልቦና አስተዳደሩ ባሉበት ጉድለቶች ኃላፊነት ላለመውሰድ ለጀርመን ችግሮች ሁሉ አይሁዶችን ተጠያቂ በማድረግ  ማሳደድ ጀመረ። አይሁዶችን ማሳደድ የግሉን የአቅም ማነስ ስሜት (የበታችነት ስሜት) ማካካሻ አድርጎታል ተብሎ ይታመናል።

ሌሎችም እንደ ሂምለር እና ጎብልስ ያሉ መሪዎች የበታችነት ስሜት ምልክቶች አሳይተው እንደነበር ይወሳል።። የበታችነት ስሜት ወደ ምቀኝነት ያመራል። ሁሉንም ነገር በመንጠቅ ወደማይጠግብ ፍላጎት ሊያጋሽብ ይችላል። ሆኖም ግን ኢጎ ልክና ወሰን የሌለው ጥልቅ ባዶነት ስለሆነ በጭራሽ ቀምቶ አይጠግብም፥ አይረካም! የኦሮሞ ጽንፈኞች እና የኦሮሙማ አርክቴክቶች የበታችነት ኮምፕሌክስ ቫይረስ ተጠቂ ይሆኑ? ምንም እንኳን ሁሉም ፋሺስቶች በባዮሎጂካል ዘረኝነት ባያምኑም በድርጊቶቻቸው ውስጥ ግን ማዕከላዊ ሚና ተጫውቷል። ናዚዝም በተለይም ለአይሁዶች ያለው አመለካከት በጣም ዘረኛ ነበር። በጀርመን ላይ ለተፈጠረው ችግር አይሁዳውያንን ተጠያቂ ሲያደርግ ከታላቁ የኢኮኖሚ ድቀት እና ከማርክሲዝም መነሳት እስከ አለም አቀፍ ካፒታሊዝም እና የስነጥበብ ማሽቆልቆል ያለምንም ልዩነት ነበር።

እነዚህ አይሁዶችን ተጠያቂ ያደረጉ ተደራራቢ ችግሮች “የመጨረሻ መፍትሄ” ተብሎ የተቀመጠው በዘር ማጥፋት የተጠናቀቀው እልቂት ነበር። ሆሎኮስት የፋሺዝም – [ባዮሎጂካል ዘረኝነት] እጅግ አስከፊ ጨካኝ ውጤት ነው። ኦሮሙማም እንደ አንድ ናዚያዊ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ተከታይ አገዛዝ፡ የሂትለርን እርምጃ ለመውሰድ የሚመኝ አረመኔ ነው። ባለፉት አምስት አመታት መንግስት ያቀነባበረው የአማራ ብሄርን የማጥፋት ተደጋጋሚ ጭፍጨፋ እና መፈናቀል የእኩይ አጀንዳቸው ምስክር ነው። ዝርዝር ይዘቶችን ለመመርመር የግራሃም ፒብልስን “ኢትዮጵያ፡ የተከዳው ለስደትና ለግድያ የተዳረገው የአማራ ህዝብ –  “Amhara People, Betrayed Persecuted And Ignored;” እንዲሁም “የጎሳ ብሄርተኝነት ስቃይ –  Ethiopia: Amhara People, Betrayed Persecuted and Ignored; እና “የዘር ሽብርተኝነት ኢትዮጵያን በማፍረስ ላይ – Ethnic Terrorism Continues to Stalk Ethiopia” መመልከት ይቻላል።

የሴማዊያን ነገዶች መጠቃት በኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ውስጥ ሴማዊ ሰዎችን ማጥቃት ለዘመናት የቆየ አረመኔነት ሲሆን በተለይም ኦሮሞዎች እንደ ባህል ቅርስ አድርገው በክብረበአል መልኩ ሁሉ ይተገብሩታል። ሴማዊ ሰውን መግደል የሚወደስ ጀግንነት መሆኑን የኦሮሞ ባህላዊ ሥርዓቶች፣ ምልክቶችና ልማዳዊ ድርጊቶች ያሳያሉ። ስለዚህ አንድ የኦሮሞ ወጣት ሴማዊውን ገድሎ የተገዳዩን መራቢያ አካል በማሳየት በህብረተሰቡ ውስጥ ለሚፈለገው ሹመት መመልመያ ያደርገዋል። ከፍተኛው የኦሮሞ ማህበረሰብ መሪ (አባ ገዳ) እራሱን እንደ መሪ ለማሳየት እስከ ዛሬ ድረስ በግንባሩ ላይ የገደለውን ወንድ ብልት አድርቆ ይለብሳል። የድርጊቱ ዝርዝሮች እና ሴማዊ ሰዎች ተመርጠው ሰለባ እንደሚሆኑ ከብዙ ህትመቶች ማግኘት ይቻላል። (28)

በመሠረታዊነት የኦሮሞ ባህል [በታሪክ] አጎራባች ማህበረሰቦችን ቀስ በቀስ በማዋሀድና ኦሮሞ በማድረግ የማያልቅ የመስፋፋት ጥማት አለው። ይህ ኦሮማይዜሽን በተለያዩ የመዋሃድ ቴክኒኮች የተከናወነ ነው። ኦሮሞዎች በቡድን አንድን ብሄር በመውረር መላውን ማህበረሰብ ኦሮሞነትን እንዲቀበል እና ኦሮምኛ እንዲናገር፣ የኦሮምኛ ባህል እንዲከተል እና የነበሩትን የራሱን ነባር እሴቶች እና ስርአቶች እንዲተው በኦሮሞዎች ይገደዳል። በዚህ መልኩ አንድ ሙሉ ብሄር ሲዋሃድ እና ኦሮሞ ሲደረግ “ሚደቻ” ይሉታል። የተወረረው ብሄረሰብ ሲዋጋቸው ደግሞ አዋቂን ሁሉ ይገድላሉ፣ የገደሏቸውን ሰዎች አካላትም ቆራርጠው ይወስዳሉ፣ ምርኮኛ ልጆችንም አሳድገው ላም እረኛ ያደርጓቸዋል።

በዚህ ሂደት ኦሮሞ ዑተደረጉ ሴማዊ ልጆች “ጉዲፈቻ” ይባላሉ። በማህበራዊ ደረጃ ያልተደራጁ እና በኢኮኖሚ ዝቅተኛ ተወዳዳሪ ማህበረሰቦች በቀላሉ ሊቆጣጠሩት በማይችሉት የኦሮሙማ ተጽዕኖ ስር ይወድቃሉ። ከዚያም እንደዚህ አይነት ማህበረሰቦች በፈቃዳቸው የራሳቸውን ኦርጅናል ማንነታቸውን ትተው ኦሮሞነትን ይቀበላሉ [ኦሮሞ ይሆናሉ]። ይህ በፈቃደኝነት የሚደረግ ውህደት “ሞጋሳ” ይባላል። የመጨረሻው እና ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ እስከ ዛሬ ድረስ ኦሮሞዎች የሚተገብሩት የባርነት ስርአት ነው። በተለመደው የኦሮሞ ባህል አንድ ሰው የጦር ምርኮኛ ከሆነ “ገርባ” ይሆናል። ገርባ አገልጋይ ለመሆን ብቻ በህይወት መኖር የሚፈቀድለት ባሪያ ማለት ነው። የገርባውን መራቢያ አካል በመቁረጥ ከሴቶቻቸው ጋር ግንኙነት መፈጸም እንደማይችል እርግጠኛ ከሆኑ በኋላ ኦሮሞ ያደርጉታል። ሃይማኖታቸውንና እሴቶቻቸውን እንዲቀበልና ቋንቋቸውን እንዲናገር ይገደዳል። ከምግብ ውጭ ግን የሚሰጠው ገንዘብም ሆነ ለውርስ የሚቀመጥለት ጥሪት የለም።  ልብስ እንኳ በራሱ ጉልበት እንስሳትን አድኖ ቆዳቸውን ገፍፎ ይለብሳል እንጅ አሳዳሪው አያለብሰውም። በዚህ ሁኔታ የሚገዙትን ባሪያ ታዲያ ገርባ ኦሮሞ ነው ይሉታል። (29)

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከለየላቸው ፀረ ሰላም ገዥ ቡድኖች ሰላም ይወለዳል ብሎ የመጠበቅ ክፉ አባዜ ይብቃ!!!

እነዚህን ቴክኒኮች በነጠላና በቅንጅት በመጠቀም ኦሮሞዎች ባለፉት ሶስት አስርት አመታት ውስጥ ብቻ 28 ብሄረሰቦችን ያስወገዱ ሲሆን ከእነሱም መካከል በዋናነት ተጠቃሾቹ ሴማዊ ጎሳዎች እና ሰዎች ናቸው። ለምሳሌ የዛይ ብሄረሰብ፡ በዝዋይ ደሴት ይኖሩ የነበሩት ባሳለፍነው  ስር አመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተወርረው ተወግደዋል። እነዚህ ሰዎች የበለፀገ የባህል ህይወት፣ ረጅም የአይሁድ እና የክርስትና ታሪክ፣ የበለፀገ የተፈጥሮ ሃብት እና ልዩ ማንነት ነበራቸው። ግራሃም ሃንኮክ (30) “የቃል ኪዳኑን ታቦት ፍለጋ” በተሰኘው ድንቅ መጽሐፉ የዛይ ሕዝብ ለ73 ዓመታት ያህል የቃል ኪዳኑ ታቦት ማረፊያ እንደነበሩ ተጠቅሷል። በዘር ሴማዊ መሆናቸውንም ገልጿቸዋል። የህዝቡ አባቶችም ቅድመ አያቶቻቸውን ወደ ሩቅ ሰሜናዊ ሴማዊ ህዝቦች አመላክተዋል። የዛይ ህዝብ ሙሉ በሙሉ የጠፋው በዙሪያው ባሉ ኦሮሞዎች ወረራ ተደርጎበት ነው።

በሐረሪ ተወላጆች ላይ በኦሮሞዎች የሚደርሰው ተደጋጋሚ ጥቃትና ወረራ ቀስ በቀስ ከተጨፈጨፈው የዛይ ብሄረሰብ ታሪክ ጋር እየተመሳሰለ ነው። ዛሬ የሐረሪ ክልል ሁለት ሶስተኛው በኦሮሞ ተወላጆች የተያዘ ሲሆን በግንብ ከታጠረው ጥንታዊና የሀረሪዎች ልዩ  መኖሪያ ከተማ ሳይቀር በብዛት እየገባ ነው። ይህ በሃረሪ ላይ ያነጣጠረው ጥቃት ኦሮሞዎች ለሴማዊ ህዝቦች ያላቸው ጥላቻ አካል ነው። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ እንደ ጃዋር መሀመድ እና በቀለ ገርባ ያሉ የኦሮሞ ህዝብ ተወካዮች እና የማህበራዊ አንቂዎች የጥላቻ ንግግሮችን፣ ስድቦችን፣ ሴማዊ ሰዎችን ለጥቃት በመፈረጅና ስም በመስጠት ያለማቋረጥ ሲናገሩ ነበር። የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ከሃያ ሺህ በላይ ህዝብ በተገኘበት በኦሮሞ የባህል በዓል ላይ በሴማዊ ነገዶች ላይ ያነጣጠረ ንግግር አድርገዋል። እሱም “የአይሁድ ወይም የአረብኛ ስም ያላቸውን አስወግድ! (31) ኦሮሞ ከሆነ የኦሮሞ ስም ሊኖረው ይገባል። አንድ ኦሮሞ ሰው አይሁዳዊ ወይም እስላም ወይም ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ኦሮሞ ነው። ሙሉ ነን። የራሳችን መሬት አለን፤ የራሳችን ስም አለን፤ የራሳችን ሀይማኖት አለን፤ የራሳችን የስፍጥረት አፈ ታሪክ አለን:: ከእነሱ ምንም መበደር አያስፈልገንም፤ እነሱን ትተን እራሳችንን የበለጠ ማጠናከር አለብን” ብሏል። ንግግሩን ተከትሎ በመላው ኦሮሚያ በሺዎች የሚቆጠሩ የሴማዊ ነገዶች እንደ ዶሮ ታርደዋል። ይህ በፓኤዝ ፔድሮ (2011) የተከተበውን አሰቃቂ (ታሪካዊ) ክስተት ያስታውሰናል።

“ኦሮሞው ብዙ ሰዎችን አርዶ ያልተለመደ ጭካኔ ፈጽሟል። ምክንያቱም ወንዶቹን እና ብዙ ሴት ልጆችን ቆራርጠዋል፤ የነፍሰ ጡር እናቶችን ሆድ በስለት  በመቅደድ ጨቅላዎችን ከማህፀናቸው አውጥተዋል። ስለዚህ የዚያ አገር ሰዎች በጣም ፈሩአቸው ስለዚህም ማንም ሊቃወማቸው አልደፈረም” እንዳለው። (32)

ኢትዮጵያ ውስጥ በሴማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ባለብዙ እርከን የተግባራት ሰንሰለት አለው። በመጀመሪያ የሴማዊ ህዝቦች እንደ አንድ ማህበረሰብ አስተሳስሮ የሚይዛቸውን የባህል እሴትና ማህበራዊ መስተጋብር  ጥቃት ይፈጸምበታል። ለምሳሌ ጨቦ ጉራጌ ማህበረሰቡን እንደ አንድ ሴማዊ ቡድን የሚለዩትን የጥቃቅንና መካከለኛ ደረጃ ማህበራዊ ተቋማትን እና ባህላዊ እሴቶችን በማጣታቸው ሙሉ በሙሉ ከኦሮሞ ጋር ከተዋሃዱ ዋና ዋና የሴማዊ ብሄረሰቦች መካከል አንዱ ነው። ጨቦን ኦሮሞ ማድረግ የተሳካለት ኦሮሙማ በተመሳሳይ ሂደት ሌሎቹን የጉራጌ አካላት ማለትም ክስታኔ፥ ሶዶ፥ ስልጤ፥ እና ሌሎቹንም በደጋ የሚኖሩትን ጉራጌዎች ለመለያየት እና እርስ በእርሳቸው እንዲቃቃሩ ለማድረግ እየሞከረ ቆይቷል። እነዚህ ማህበረሰቦች በጉራጌ ብሔር ጥላ ስር ያሉ ሴማዊ ህዝቦች ናቸው። አሁን አገዛዙ ጥረት እያደረገ ያለው እነዚህን ህዝቦች ወደ ኦሮሞነት እንዲሸጋገሩ ወይም እንዲጠፉ የሚያደርጉ ገራም ስልቶችን በመጠቀም ነው። የቋንቋ ፅሁፎቻቸውን ጨምሮ ብዙ ባህላዊ ነገሮችን ለመቀየር ጫና እየተደረገ ይገኛል።

አሁን ጉራጌ በብዙ ግንባሮ በሰይፍ ጫፍ ላይ ተደቅኗል። የኦሮሞ ልሂቃን ጉራጌን ለማጥቃት ከውስጥ ሆነው ጉራጌን ሊያዳክሙላቸው ከሚችሉት የቀቤና ቡድኖች ጋር የስርዓት ጥምረት ፈጠሩ። የቀቤና ብሄረሰብ በቅርቡ የቋንቋቸውን ኦፊሴላዊ ፊደላት ወደ ቁቤ ቀይሯል። ይህ የኩሽ ህዝቦች ጥምረት በሚል አጀንዳ የሚንቀሳቀስ ጉራጌውን የማጥቂያ ውስጣዊ አሰላለፍ ነው። ቀደም ብሎ ወላይታ፣ ሲዳማ፣ ጌዲዮ እና ኦሮሞ የኩሽ ህብረት አባላት ሲሆኑ በዋናነት የኦሮሙማን አጀንዳዎች ለመፈጸም የሚደረግ ትብብር ነው። የኩሽ ጥምረት አላማ ኦሮሙማ በሚያደርገው ጅምላ ግድያ ላይ ሴማዊ ያልሆኑ ሰዎችን ተደባልቀው ሰለባ እንዳይሆኑ መጠበቅ ነው። ህብረቱ ከሴማዊ ኢትዮጵያውያን ጋር ተሳስረው የሚኖሩትን ሰዎቻቸውን የመለየት እና የማስገንዘብ ስራ ይሰራል። ልየታውን ተከትሎ ታዲያ ትልቁ ጥቃት የሚደርሰው በሀገሪቱ ውስጥ ትልቁ ሴማዊ ቡድን በሆነው የአማራ ህዝብ ላይ ነው። ጥቃቱም ለምእተ አመታት በዝምታ ቀጥሏል።

ይህ ግፍ እና ሴማዊያንን አላማ ያደረገው ግድያ ማህበራዊ ህይወት አደረጃጀትና አስተዳደራዊ ርዕዮተ ዓለም ዋና አካል ነው። ሴማውያንን ከኢትዮጵያ አጽድቶ፥ ኩሻውያንን ኦሮሞ አድርጎ፥ የኦሮሞ ብቻ የሆነች ሀገር ይመኛሉ። ለዚህ ራዕይ ዋና ስልት አድርገው የሚጠቀሙት በገዳ ስርአት የሚፈጸመውን የመስፋፋት ልማድ ሲሆን በመስፋፋቱ ሂደት የሚቀርቧቸውን ህዝቦች ከፋፍለው ይገነጣጥላሉ ከዚያም የተበታተኑ ክፍሎችን በመውረር ያጠፋሉ። በመሆኑም ሴማዊ ሰዎችን የማጥፋት ፍላጎታቸውና ኦሮሞን የማስፋፋቱ ስራ ተሰናስሎ በባህላዊ ስርአት ተቀባይነት አግኝቶ እንዲቀጥል ረድቷቸዋል። ድርጊቱ አረመኔያዊ ኋላ ቀርነት ቢሆንም በኦሮሞ ባህላዊ የሞራል እሴት ሥርዓት ውስጥ በጣም የተከበረ ስለሆነ የቀን መቁጠሪያዎች፣ በዓላት፣ ማህበራዊ ደረጃዎች/ማዕረጎች እና በመሳሰሉት አሠራሮች ተቀርጿል።

አሁን ከዚህ ዓሐዕኀዓኧዒኘዓ ጠዓዒኸዓኧዒ ዳራ የመጣ አንድ የፖለቲካ አካል በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ስልጣን ተቆጣጥሯል። እነዚህ የፖለቲካ ድርጅቶች በአብይ አህመድ የሚመሩ እና ሴማዊ ህዝቦችን ለማፅዳትና የኦሮሞ ስርወ መንግስት ለመመስረት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልፅ የሆነ የዘር ማጥፋት ፕሮግራም ይዘዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ በቀሩት ሴማዊ ሰዎች ላይ የተለመደ ጦርነት ተከፍቷል። በተለይ በአማራ እና በጉራጌ ህዝብ ላይ። የኩሽ ማህበረሰቦች ሴማዊ ሰዎችን ለመግደል ህብረት ከፈጠሩ ሴማዊ ሰዎች እራሳቸውን ለመከላከል እውነተኛ ህብረት እንዳይፈጥሩ የሚያደርጋቸው አመክንዮ ታዲያ ምንድን ነው? ከዚህ እልቂትስ ለመትረፍ ሌላ ምን አማራጭ አላቸው?

በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለው መገለል፥ ስደት እና ጭፍጨፋ በአዶልፍ ሂትለር ዘመን ደረጃ በደረጃ በአይሁዶች ላይ ተተግብሯል። በመንግስት የተደገፈው የአማራው ጥላቻ፥ ፀረ አማራ ፖሊሲዎች እና አዋጆች እንዲወጡ ምክንያት ሆኗል። አላማቸው አማራው እንደ መንግስት ለሶስት ሺህ አመታት ሲጫወተው ከነበረው ማዕከላዊ ሚና በተቀናጀ መንገድ ማግለል፤ ከ2000 ዓመታት በላይ የክርስትና እና የእስልምና እምነቶች ሞግዚት መሆኑ፣ የመጽሐፍ ቅዱሳዊ እና የቁርዓን ባህሎች እና ሀገሪቱ በአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት ሆና በዓለም ዙሪያ ላሉ ሁሉ ጥቁሮች የሰጠችው ተስፋና ኩራት፥ እና ሌሎቹም የታሪክና የባህል ይዘቶች የፈጠሩባቸው ቅናት እና የዝቅተኝነት ስሜት አማራውን ለማጥፋትና ታሪኩን ለመቀማት አነሳስቷቸዋል። ይህም ጥቃት ከ1941 እስከ 1945 በጀርመን አይሁዶች ላይ ከተፈፀመው ጥቃት ጋር ሁለንተናዊ መመሳሰል አለው። በአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰው ግፍ በህወሓት አገዛዝ በጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ተጀምሮ አሁንም በጠ/ሚ አብይ አህመድ ተባብሶ የቀጠለ ነው። (33)

ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ወደ 9.5 ሚሊዮን የሚጠጉ አይሁዳውያን በአውሮፓ ይኖሩ ነበር። ጦርነቱ ሲያበቃ ናዚዎች በማጎሪያ ካምፖች፥ በፖግሮም እና በጌቶዎች ወደ 6 ሚሊዮን አይሁዳውያንን በጅምላ ገድለዋል። ናዚዎች Endlösung ወይም Final Solution የሚለውን ቃል ለ”የአይሁድ ጥያቄ” እንደ “መልስ” ተጠቅመውበታል። አዶልፍ ሂትለር እ.ኤ.አ. በ1922 ጅምላ ጭፍጨፋ ለመፈጸም ያለውን ምኞት ለጋዜጠኛ ጆሴፍ ሲኦል “አንድ ጊዜ እኔ በስልጣን ላይ ከሆንኩ የመጀመሪያ እና ዋና ስራዬ አይሁዶችን ማጥፋት ነው” በማለት ፍንጭ ሰጥቶ ነበር። የዚህን አቻ ንግግር በሀገራችን መሪዎች ሲደረግ ለአማራዎች በጣም የተለመደ ነው። አብይ አህመድም የተናገረው በተለየ መንገድ ይሁን እንጅ አማራውን ማጥፋት እንደሚፈልግ አስቀድሞ ቃል የገባለት ቡድን አለው። አብይ አህመድ እና ባለስልጣኖቹ ዋነኛ ጠላቶች አማሮች እና ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በተናገሩት መሰረትም ቤተክርስትያንን እና አማሮችን (ሴማውያንን) ማጥፋት ጀምረዋል። ለፉህረር ያላቸውን ታማኝነት ለማሳየት በዙሪያቸው ያሉ አይሁዶችን ለመግደል መግደል የሚፈልጉ ሰዎች መኖራቸውን ባወቀ ጊዜ፡ ሂትለር የአይሁዶችን ችግር ወደ “ጽንፍ” ወስዶታል። አብይ አሁን እነዚህን አይነት ሰዎች አሰልፏል። አብይ አድማጮቹ ሊሰሙት የሚፈልጉትን በውሸት እንዴት ማሸግ እንዳለበት የሚያውቅ ልዩ ተሰጥኦ ያለው ተናጋሪ ነው። ውሸቱ ግን በአጭር ስለተገለጠበት፡ አሁን አገዛዙን በውሸት ማስቀጠል ስላልቻለ በሽብር እየገዛ ነው።

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈፀመ ያለው የሴም ነገዶች ጭፍጨፋ ግልጽ  የዘር ማፅዳት ሲሆን አላማውም የኩሽ ኢምፓየር ለመመስረት እንደሆነ በወንጀል ምርምሩ የተሳተፉ የህግ ባለሞያዎች ገልጸውታል።  እንደ ኩሽ ሚዲያ እና የኦሮምኛ መዛግብት ትረካ ከሆነ ሴማዊ ነገዶች (በተለይም አማራዎች፥ ጉራጌዎችና ትግራውያን) የኩሽ ተወላጆችን ቅኝ ገዝተዋል ተብሎ እጅግ የሚገርም ጠማማ ታሪክ ተጽፏል። በዚህም ትርክት ምክንያትም በኩሻውያን በተነሳ ጥላቻና የበቀል እርምጃ ባለፉት 4 ዓመታት የዘር ማጥፋት እና የጦር ወንጀሎች ተፈጽመዋል። ወደ ሦስት ሚሊዮን ለሚሆን ሕዝብ ሞትና ከ4 ሚሊዮን በላይ አማሮች መፈናቀል ምክንያት ሆኗል። (34) ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲነቃና ይህን እብደት እንዲያስቆም ስንት ሞትና ስንት ተፈናቃይ መመዝገብ አለበት? (35)

የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ሻለቃ ዳዊት ጊዮርጊስ እንደሚሉት ይህ የኩሽቲክ ጦርነት በሰሜናዊ ሴማውያን ላይ የተካሄደው እጅግ አረመኔያዊ በሆነ መንገድ ነው – በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ የጭካኔ አይነት ነው ይላሉ። የጥላቻ ጥግ የታየበት ጥቃት ነው የተፈጸመው። በኦነግ መሪነት የኩሽቲክ እንቅስቃሴ የሚለው ጦርነት ኢትዮጵያ ውስጥ ቢጀመርም በሂደት ግን ከኢትዮጵያ አልፎ ኬንያ፣ ሱዳንና ሶማሊያ ድረስ መግባቱ የማይቀር ነው።

ማጠቃለያ

ኦሮሙማን አደገኛ የሚያደርገው የተለያዩ ባህላዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ የሕይወት ዘርፎች የሚሰባሰቡበትን ልዩ የኦሮሞ ወጎችና እሴቶችን ለማስተዋወቅ ባህላዊና ማኅበራዊ ምኅዳሩን ለመለወጥ መሻቱ ነው። ይህን የባህልና ማህበራዊ ልማት መሻት በራሱ ምንም ስህተት ወይም ችግር የለበትም። ነገር ግን ኦሮሙማ እንቅስቃሴውን በናዚያዊ መንገድ ነው ማስፈጸም የጀመረው እና ግቡን ማሳካት የሚፈልገው። ለናዚ ጀርመን ሶስተኛው ራይክ የዘር ማንነቷን በማጥራት እና በማዋሃድ ሀገሪቱን ወደ ቀድሞ ክብሯ መመለስ እንደነበረው ሁሉ ኦሮሙማም የኦሮሞን ጎሳ ማንነት በማጥራት እና በማዋሃድ “የገዳን ክብር ለመመለስ” ይሞክራል። (36) በዚህ ሁሉ ሂደት ታዲያ የአማራው ተወላጅ በተደራራቢ ጥቃቶች ቀዳሚ ተጎጂ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከመቅረት መዘግየት በሚል እሳቤ የቀረበ ጭፍን ጥላቻ አስተያየት አይደለም ሊሆንም አይችልም!! - አኒሳ አብዱላሂ

በመጀመሪያ የጭካኔ ወንጀሎች ኢላማ (የመጀመሪያ ደረጃ ተጎጂነት) ነው፤ በመቀጠል በአማራ የደረሰውን ጥቃት ሌሎቹ ምናልባትም ጥቃት ያደረሱት ኃይሎች  “ከአማራው ይልቅ እኛ ነን የተጎዳነው ይሉና ጩኸቱን ይቀሙታል፡ (ሁለተኛ ደረጃ ተጎጅነት) ይደርስበታል። በዚህም ሳይበቃቸው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአማራ ላይ ስለደረሰው ጭፍጨፋ መረጃ እንዳይደርሰው የሀሰት መረጃዎችን በመፈብረክ በብዛት ‘የተማረ ዳያስፖራ’ እየተባለ የሚጠራውን ትውልደ ኢትዮጵያዊ በመጠቀም ወንጀሉ ተድበስብሶ እንዲቀርና ፍትህ እንዳይጠየቅበት በማድረግ ለሶስተኛ ጊዜ አማራውን ይበድሉታል። በመሆኑም አሁን በዐማራው ላይ እየደረሰ ያለውን ሰብዓዊ ቀውስና የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የዓለም ሚዲያና የሕዝብ አስተያየት ደንታ ቢስ ሁኖበታል። ምንም እንኳ የጅምላ ግድያውና የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋው የጅምላ መቃብሮችን ጨምሮ የእነዚያን ግፍና ጭፍጨፋዎች ትክክለኛ አሀዛዊ መረጃ ቢቀርብም ትርጉም መስጠት ተስኗቸዋል። አራተኛ ደረጃ ጉዳቱ እና ትውልድ ከዚህ ጭፍጨፋ ሊማረው የሚገባውን ጥፋት የሚሸፍነው ደግሞ በጽንሰ ሀሳብ ማብራሪየዓ ደረጃ የአማራውን ሰለባ መሆን ውድቅ የማድረግ ሙከራዎች ናቸው። አሁን በርካታ ተንታኞች “አንድ ማህበረሰብ የሚገባውን ማህበራዊ እውነት ነው የሚጋፈጠው” የሚል የአማራውን እልቂት ተገቢ እርምጃና በራሱ በአማራው ድክመት የተከሰተ አድርጎ በመውሰድ የወንጀሉ ፈጻሚዎች ተጠያቂ ሊደረጉበት ሲገባ ጉዳቱ ፍትህ የማይሰጥበትና በታሪክም የሚረሳ እንዲሆን እየሰሩ ነው። በእርግጥ አማራው የተቃጣበትን እልቂት አስቀድሞ ተረድቶ ተደራጅቶ መመከትና እራሱን ማዳን ነበረበት፤ ያለምንም ወንጀል የተጨፈጨፈን ንጹህ ህዝብ “የሚገባውን ማህበራዊ እውነት ተጋርጧል” ብሎ ማለፍ ምን ያህል ክፋት ነው?!

በናዚ ስልት እየተፈጸመ ያለው “አማራፍሬ”- በዋናነት አማራውን ከኦሮሚያ የማጥፋት ጭፍጨፋ፡ በዘግናኝ ሁኔታ እየተካሄደ ቆይቷል። የ”አማራፍሬ” ዘመቻ እስካሁን አመማራውን በማጥፋት ላይ ትኩረት ቢያደርግም በመሰረታዊነት ግን እራሳቸውን በኢትዮጲያዊነት የሚገልጹና የሚያምኑትን የሚመለከትና ጊዜያቸውን ጠብቆ በእነርሱም ላይ ጭፍጨፋው መደረጉ የማይቀር መሆኑን ማስታወስ ጠቃሚ ነው። (37) “አማራፍሬ” ከ ‘Judenfrei’ ጋር ተመሳሳይ ነው። (38) “አማራፍሬ” በ1991 የተጀመረውን የወያኔ ፖሊሲ በአቢይ እና በሽመልስ አገዛዝ በጉልበት በመከተል ኦሮሚያን እና ሌሎች ክልሎችን አማራ የሌለባቸው ለማድረግ [ለማፅዳት] ተጠቅመውበታል። ይህም ኢትዮጵያን ለማጥፋት ዋናው ሂደት እንደሆነ በማመን የተተገበረ ነው። ተከታትሎም የሴማዊ ህዝቦችን ከሀገሪቱ ለማጥፋት እየተተገበሩ ያሉት ወንጀሎች፦ ታሪክ ማጥፋት፣ ልሳነ [ቋንቋና የጽሁፍ ሀብቶችን] ማጥፋት፥ ቅርሶችን ማውደም፥ እና በመጨረሻም ዘር ማጥፋት ናቸው።

References

  1. Ethiopia: The Final Solution (by Dawit Giorgis ) (zehabesha.com)
  2. Aseffa Jalata: Urban centers in Oromia, consequesnces of Spacial concentration of power in Multinational Ethiopia: Journal of Oromo studies, Vol. 17 no 2 (July 20lO): Lata, L’Peculiar Challenges to Oromo Nationalism;’ in Oromo Nationalism and the Ethiopian Discourse. Edited by Asafa Ialata, Lawrenceville, NJ: The Red Sea Press, (1998)
  3. Norbert Götz. Ungleiche Geschwister: Die Konstruktion von nationalsozialistischer Volksgemeinschaft und schwedischem Volksheim. Baden-Baden: Nomos, 2001; Peter Fritzsche. Life and Death in the Third Reich. President and Fellows of Harvard College, 2008. p. 38.
  4. Jason Stanley, professor of philosophy at Yale University and author of “How Fascism Works(opens in new tab)” (Random House, 2020) told All About History(opens in new tab) magazine.
  5. The extremists say that Gada System reflects Oromo’s cultural, political, economic, social, and religious traditions. Consequently, Oromummaa became a wholistic movement.
  6. Oromummaa’s First Targets of Destruction are the Oromo People and Culture (zehabesha.com) (Yonas Biru, PhD)
  7. https://addisinsight.net/oromummaas-religion-cleansing-and-cultural-evilgelization-project/ ((Yonas Biru, PhD)
  8. A journal published by the International African Institute suggests it is an Oromo word (adopted by neighbors), for there is a word, gala, meaning ‘wandering’ or ‘to go home’ in their language. The Oromo never called themselves Galla and resist its use because the term is considered derogatory.
  9. Juxon Barton (September 1924), The Origins of the Galla and Somali Tribes, The Journal of the East Africa Natural History Society, No. 19, pages 6–7
  10. Herbert S. Lewis. “A Galla Monarchy: Jimma Abba Jifar, Ethiopia 1830–1932″. Madison: The University of Wisconsin Press, 1965.
  11. In June 2023, the OLF is celebrating its 50th anniversary. As the nominal leader Dawud Ibsa claimed half of the goal is achieved. Ethiopia is a nation without a state and a government for that matter. The Civil war has killed over a million so far. Over two million non-Oromos have been wiped out from the Oromia region. The orthodox church is officially banned. The economy has collapsed. Abiy Ahmed leads the official government from the old palace in Addis Ababa. They’re building a new palace too. The actual OLF government rules the rest of Ethiopia. The TPLF has succeed since 2018. It’s been functioning as its own state since then.
  12. https://shegerpost.blogspot.com/2023/06/httpsshegerpost.blogspot.comafter-50-years-of-bloody-campaign-olf.html
  13. https://addisinsight.net/oromummaas-religion-cleansing-and-cultural-evilgelization-project/
  14. A Cultural History of Genocide, 6 volumes edited by Paul R. Bartrop, Bloomsbury Academic, London and New York, 2021(Munson, H. (2023). A Cultural History of Genocide, 6 volumes: edited by Paul R. Bartrop, Bloomsbury Academic, London and New York, 2021)
  15. Ibid
  16. The Effort to Crown Gadaa, Irrecha and Waaqeffanna as Unifying Cultures. As a tribal society, Oromo is culturally, religiously, and socially diversified and fragmented. The Oromo of Shewa has a lot more in common with the Amhara of Shewa than with the Oromo of Wellega. The same way, the Muslim Oromos of Arsi have little in common with the Oromo of Shewa or Wellega who are mostly Christians. There is no Oromo-centric culture that ties all Oromos together. The social engineers of Oromummaa saw this as a hurdle to build a unified national movement.
  17. “The Oromummaa Politics: Weaponized with Lies and Soaked in Blood” and “Oromummaa is a Low Grade Nazification Movement.”
  18. Adolf Hitler: Hitler’s Second Book (New York 2003) XXI
  19. https://borkena.com/2023/06/03/oromummaas-religion-cleansing-and-cultural-evilgelization-project/
  20. Aseffa Jalata, Fighting Againist the Injustice of the state and Globalization: comparing the African American and Oromo movement, (2001). Aseffa Jalata, in and out of Africa: Journal of Black studies, Vol.XX no.X, (2008).
  21. What makes Oromummaa dangerous is that it is anti-Christianity and anti-Islam in a country where the two Abrahamic religions account for over 90 percent of the nation’s population. In recent days Oromummaa’s ethnic cleansing endeavor has been elevated to religion/religious cleansing crusade. A 398-page study from the University of South Africa notes Professor Asafa Jalata, the Godfather of Oromummaa, “is hesitant to affirm Islam as having any rightful place within Oromo identity” and blames the processes of “Abyssinianization and Christianization” of Oromos as racist endeavors.
  22. Páez, Pedro (2011), History of Ethiopia, 1622, vols 1 and 2 [Hakluyt Society, 3rd Series], ed. Isabel Boavida and Hervé Pennec, trans. Manuel João Ramos, Burlington, VT: Ashgate Publishing for the Hakluyt Society. In A Cultural History of Genocide, 6 volumes: edited by Paul R. Bartrop, Bloomsbury Academic, London and New York, 202.
  23. https://www.libraryofsocialscience.com/ideologies/resources/koenigsberg-ideology-perception/
  24. Oromummaa is a Low-Grade Nazification Movement – Addis Insight. By Addis Insight May 15, 2023.Yonas Biru, PhD
  25. Greater Ethiopia: The Evolution of a Multiethnic Society (Donald N. Levine)University of Chicago Press, 2000 – 231 pages).Greater Ethiopia combines history, anthropology, and sociology to answer two major questions. Why did Ethiopia remain independent under the onslaught of European expansionism while other African political entities were colonized? And why must Ethiopia be considered a single cultural region despite its political, religious, and linguistic diversity?
  26. Jalata, Asafa (1993), Oromia and Ethiopia: State Formation and Ethnonational Conflict, 1868–1992, Boulder, CO: Lynne Rienner Publishers.
  27. https://borkena.com/2023/06/22/is-this-the-end-of-greater-ethiopia/?fbclid= IwAR1aarKtY1dE9ZDvIFEe2zwp4UYp7-1QL7BCfSWklsBiWNG4HYkMp54Zq6c
  28. See Páez, Pedro (2011), History of Ethiopia, 1622, vols 1 and 2 [Hakluyt Society, 3rd Series], ed. Isabel Boavida and Hervé Pennec, trans. Manuel João Ramos, Burlington, VT: Ashgate Publishing for the Hakluyt Society. A Cultural History of Genocide, 6 volumes: edited by Paul R. Bartrop, Bloomsbury Academic, London and New York, 202.
  29. Davidson, Lawerence (2012), Cultural Genocide, New Brunswick, NJ: Rutgers University Press; bin Uṯmān, Šihāb ad-Dīn Aḥmad bin Abd al-Qāder bin Sālem (2003), Futūḥ al-Ḥabaša: The Conquest of Abyssinia [16th century], ed. and trans. Paul Stenhouse, Hollywood: Tsehai Publishers.
  30. Hancock, Graham (1992).The Sign and the Seal: The Quest for the Lost Ark of the Covenant. New York: Crown.
  31. Walker, “Martin Luther’s Dirty Little Book: On the Jews and their Lies- a Precursor to Nazism:’ NoBeliefs.com, http://nobeliefs.com/luther.htm.
  32. Páez, Pedro (2011), History of Ethiopia, 1622, vols 1 and 2 [Hakluyt Society, 3rd Series], ed. Isabel Boavida and Hervé Pennec, trans. Manuel
  33. Ethiopia : The Final Solution (by Dawit Giorgis ). https://borkena.com/2023/04/12/ethiopia-the-final-solution-by-dawit-giorgis/
  34. See Berhanu’s series of articles published On Euro Asia Review.
  35. Ibid
  36. Oromummaa’s Religion Cleansing and Cultural Evilgelization Project. Oromummaa’s Religion Cleansing and Cultural Evilgelization Project – Addis Insight
  37. The Abiy Ahmed & Shimelis Abdissa Lawless Regime and “Amharafrei”  (zehabesha.com)
  38. Literally translated, judenfrei means “free of Jews.” This was the term the Nazis used to designate areas where every single Jew had been killed or rounded up for deportation. Massacres like the Erntefest were designed to create judenfrei areas in Poland. x

 

Share