March 14, 2023
2 mins read

የኦሮሚያ ክልል የአባይን ግድብ የመጠቅለል እቅድ ፡ በኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል እና በቤኒሻንጉል ክልል ልዩ ኃይል መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ነው

የኦሮሚያ ክልል መንግስት ታላቁ የህዳሴ ግድብን ወደ ኦሮሚያ ለመጠቅለል ጫፍ ደርሷል። የግድቡ ውሃ የሚተኛበት መሬት የማስፋፊያ ስራ እየተሰራ ነው።
ለጉባ አዋሳኝ በሆነችው ሸርቆሌ ወረዳ ልዩ ስሙ አውል ቤጎ በተባለ አከባቢ በደን ምንጣሮ ከተሰማሩት 3000 በላይ ወጣቶች መካከል ሙሉ በሙሉ በሚያስብል ደረጃ የኦሮሞ ተወላጆች ናቸው።(የአማራ ተወላጆች ስራውን ለቀው እንዲወጡ ተደርገዋል)። በስራው የተሰማሩት የኦሮሞ ተወላጆቹ ወታደራዊ ስልጠና የተሰጣቸው ናቸው ተብሏል።
በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የኦነግ ታጣቂዎች ጋር ሰፊ ግንኙነት እንዳላቸውም ተጠቁሟል። በተጨማሪም ለጉባ ወረዳ በቅርብ ርቀት በሚገኘው ልዩ ስሙ ሲርባባይ በተባለ አከባቢ በኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል እና በቤኒሻንጉል ክልል ልዩ ኃይል መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ነው። ከዚህ አልፎ ግድቡ በሚገኝበት ጉባ ወረዳ እና በምዕራብ ወለጋ ዞን መካከል የሚገኘው የካማሺ ዞኑ ኦዳ ቡልዱ ጉሉ ወረዳ ነዋሪዎች አከባቢያችሁ ወደ ኦሮሚያ ክልል ስለተካለለ በአስቸኳይ ለቃችሁ ውጡ የሚል ትዕዛዝ ከኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል እንደተሰጣቸውም ተሰምቷል። የአማራ ድምፅ ሚድያ አንድ የቤኒሻንጉል ክልል ከፍተኛ አመራርን ጨምሮ ነዋሪዎቹን እንዲሁም በደን ምንጣሮው የተሰማሩ ወጣቶችን አነጋግሯል። ዝርዝሩን ይከታተሉ።
ምንጭ የአማራ ድምፅ

https://youtu.be/R9xEyI8Kut4

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop