March 14, 2023
2 mins read

የኦሮሚያ ክልል የአባይን ግድብ የመጠቅለል እቅድ ፡ በኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል እና በቤኒሻንጉል ክልል ልዩ ኃይል መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ነው

180766
የኦሮሚያ ክልል መንግስት ታላቁ የህዳሴ ግድብን ወደ ኦሮሚያ ለመጠቅለል ጫፍ ደርሷል። የግድቡ ውሃ የሚተኛበት መሬት የማስፋፊያ ስራ እየተሰራ ነው።
ለጉባ አዋሳኝ በሆነችው ሸርቆሌ ወረዳ ልዩ ስሙ አውል ቤጎ በተባለ አከባቢ በደን ምንጣሮ ከተሰማሩት 3000 በላይ ወጣቶች መካከል ሙሉ በሙሉ በሚያስብል ደረጃ የኦሮሞ ተወላጆች ናቸው።(የአማራ ተወላጆች ስራውን ለቀው እንዲወጡ ተደርገዋል)። በስራው የተሰማሩት የኦሮሞ ተወላጆቹ ወታደራዊ ስልጠና የተሰጣቸው ናቸው ተብሏል።
በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የኦነግ ታጣቂዎች ጋር ሰፊ ግንኙነት እንዳላቸውም ተጠቁሟል። በተጨማሪም ለጉባ ወረዳ በቅርብ ርቀት በሚገኘው ልዩ ስሙ ሲርባባይ በተባለ አከባቢ በኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል እና በቤኒሻንጉል ክልል ልዩ ኃይል መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ነው። ከዚህ አልፎ ግድቡ በሚገኝበት ጉባ ወረዳ እና በምዕራብ ወለጋ ዞን መካከል የሚገኘው የካማሺ ዞኑ ኦዳ ቡልዱ ጉሉ ወረዳ ነዋሪዎች አከባቢያችሁ ወደ ኦሮሚያ ክልል ስለተካለለ በአስቸኳይ ለቃችሁ ውጡ የሚል ትዕዛዝ ከኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል እንደተሰጣቸውም ተሰምቷል። የአማራ ድምፅ ሚድያ አንድ የቤኒሻንጉል ክልል ከፍተኛ አመራርን ጨምሮ ነዋሪዎቹን እንዲሁም በደን ምንጣሮው የተሰማሩ ወጣቶችን አነጋግሯል። ዝርዝሩን ይከታተሉ።
ምንጭ የአማራ ድምፅ

https://youtu.be/R9xEyI8Kut4

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Justice 1 1
Previous Story

የሽግግር ፍትህን ለማሰብ የሚቻለው ከትናንቱ ዛሬ የተሻለ በጎነት ሲኖር ነው (ገለታው ዘለቀ)

Adanch ababe 1 1
Next Story

“ከአንዳንድ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት መንግስትን በመጣል በኃይል ስልጣን ለመቆጣጠር ያለመ ነው”- ከንቲባ አዳነች አበቤ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop