January 6, 2023
5 mins read

ባሕር ዳር ላይ የሚቀዝነው ኢህአዴግ (ከአሁንገና ዓለማየሁ)

Bahird Dar PP party meetingበተረኝነት የሚፈራረቁት የጎሳ ድርጅቶች ራሳቸውን እንጂ የሚምሉበትን ሕዝብ አይወክሉም። ራሳቸው ተሰባስበው ወይም ሌላ ጌታ አሰባስቧቸው የቆሙ ጨቋኝና ጨፍላቂ ድርጅቶች እንጂ ዲሞክራሲያዊ አይደሉምና። አካሄዳቸውም እንወክለዋለን ያሉትን ሕዝብ የማስጠላት፣ የመነጠልና ጨቁኖ እና አስደንብሮ ሌላውን የመጨቆኛና የማጥቂያ መሣሪያ አድርጎ መገልገል ነው።

ከአሥር አመት በፊት ነው። አውሮፕላን ማረፊያው ደርሼ የመታሰቢያ ፎቶ ልነሳ ቀና ስል “ግንቦት ሃያ አውሮፕላን ማረፊያ” የሚል መፈክር ተጽፎበት አየሁ። እንደማቅለሽለሽ አደረገኝ። ባሕር ዳር ነው ቦታው። እውነት ባሕር ዳር ነው? ብዬ ራሴን ጠየቅሁ። የአማራ ክልል ብላ ወያኔ በሰየመችውና በዋና ከተማው በባህር ዳር ኢትዮጵያ የፈረሰችበት፣ አማራ ከነነፍሱ የተቀበረበት፣ የሩዋንዳ ጂኖሳይድ፣ የዮጎዝላቪያ ፍርሻ ውጥኖች በኢትዮጵያ መሠረታቸው የተጣለበት ዘመን መባቻ በሆነው በግንቦት ሃያ መሰየሙ ያጥወለውላል።

ይሄንን አስቀያሚ ስሜት ባሕር ዳር ላገኘኋቸው የአካባቢው ተወላጆች ስገልጽላቸውና እነሱም በአማራ መሪነት የተሰየሙት ባእዳን ላይ ከፍተኛ ቁጣ ሲገልጹ ስሰማ ሰነበትኩ።  መልሱ ጉዞዬ ቀን በረከት ስምኦን ያለምንም አጀብና ጥበቃ እየተጎማለለ ባሕርዳር ኤርፖርት መጥቶ እኔው በምሄድበት አውሮፕላን ከፊት ተቀምጦ ሲሄድ አየሁ። “አይ አማራ ምስኪኑ!” ይላል ዘመድኩን።

የአውሮፕላን ማረፊያውን ስያሜ ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ወያኔ ቁምጣውን ገልቦ ቅዘኑን በአማራው ላይ እንደተጸዳዳበት ዐይነት ስሜት ነው። ይቅርታ ለአገላለጹና ለቋንቋው።  እውነተኛውን ስሜት ለማሳየት በሚል ነው።   ዛሬም የአቢይ አህመድ  የአማራ  ማረጃ ቆንጨራ  የሆነው ሽመልስ  አብዲሳ አማራ ባረደ ቁጥር  ባሕር ዳር  እየሮጠ  ካባ  አልብሱኝ  ማለቱ  አልበቃው  ብሎ፣  ባሕር ዳር  ገብቶ  የብአዴን ስብሰባ ሲመራ  ውሏል።  የ ሽመልስ ጦር በዚያው ሰዐት በአንገር ጉተን እና ሌሎችም የወለጋ  ቀበሌዎች የተለመደውን የአማራ ጭፍጨፋ እያካሄደ በደም ጎርፍ እየዋኘ ያለበት ጊዜ ነው።  አማሮች በወለጋ የጅምላ መግደያ መጋዘኖች እየተዘጋጀላቸውና የጅምላ መቃብር እየተቆፈረላቸው ያለበት ወቅት ነው።  ከባሕር ዳር በመቶ ኪሎሜትር ርቀት በየጫካው የተበተኑ የወለጋ ተፈናቃዮች አባ ከና ያላቸው ሰው የለም።

በአቢይ ሕወሃት ጦርነት በቢሊዮን ብር በወደመው የአማራ ክልል እና በሚሊዮን አሃዝ ባለቀው የአማራ ልጅና ገበሬ እልቂትና ውድመት የሽመልስ ቡድን “ድል ተመዘገበ” እያለ ቦላሌውን ገልቦ ሲቀዝንበት ውሏል። በብአዴን ላይ። ብአዴን ደግሞ በአማራ ስም ስለሚንቀሳቀስ የተዋረደው በእጅ አዙር ማን እንደሆነ ግልጽ ነው። አዎ ድል አስመዝግበዋል። ሀገር አፍራሾቹ ከፍርሻ አጀንዳቸው አኳያ። ያንን ውርደትና ውድመት ግን ተበዳዩን “ድሌ” ነው ብለህ ተቀበል ማለት በሰው ገበታ ላይ ከማስታወክ ይበልጥ ይቀፋል።

ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ይላሉ አበው። ጊዜ የሰጠው ድንጋይማ ምንኛ ይበረታ!

ታኅሣስ 27፣ 2015

አሁንገና ዓለማየሁ

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop