January 6, 2023
5 mins read

ባሕር ዳር ላይ የሚቀዝነው ኢህአዴግ (ከአሁንገና ዓለማየሁ)

Bahird Dar PP party meetingበተረኝነት የሚፈራረቁት የጎሳ ድርጅቶች ራሳቸውን እንጂ የሚምሉበትን ሕዝብ አይወክሉም። ራሳቸው ተሰባስበው ወይም ሌላ ጌታ አሰባስቧቸው የቆሙ ጨቋኝና ጨፍላቂ ድርጅቶች እንጂ ዲሞክራሲያዊ አይደሉምና። አካሄዳቸውም እንወክለዋለን ያሉትን ሕዝብ የማስጠላት፣ የመነጠልና ጨቁኖ እና አስደንብሮ ሌላውን የመጨቆኛና የማጥቂያ መሣሪያ አድርጎ መገልገል ነው።

ከአሥር አመት በፊት ነው። አውሮፕላን ማረፊያው ደርሼ የመታሰቢያ ፎቶ ልነሳ ቀና ስል “ግንቦት ሃያ አውሮፕላን ማረፊያ” የሚል መፈክር ተጽፎበት አየሁ። እንደማቅለሽለሽ አደረገኝ። ባሕር ዳር ነው ቦታው። እውነት ባሕር ዳር ነው? ብዬ ራሴን ጠየቅሁ። የአማራ ክልል ብላ ወያኔ በሰየመችውና በዋና ከተማው በባህር ዳር ኢትዮጵያ የፈረሰችበት፣ አማራ ከነነፍሱ የተቀበረበት፣ የሩዋንዳ ጂኖሳይድ፣ የዮጎዝላቪያ ፍርሻ ውጥኖች በኢትዮጵያ መሠረታቸው የተጣለበት ዘመን መባቻ በሆነው በግንቦት ሃያ መሰየሙ ያጥወለውላል።

ይሄንን አስቀያሚ ስሜት ባሕር ዳር ላገኘኋቸው የአካባቢው ተወላጆች ስገልጽላቸውና እነሱም በአማራ መሪነት የተሰየሙት ባእዳን ላይ ከፍተኛ ቁጣ ሲገልጹ ስሰማ ሰነበትኩ።  መልሱ ጉዞዬ ቀን በረከት ስምኦን ያለምንም አጀብና ጥበቃ እየተጎማለለ ባሕርዳር ኤርፖርት መጥቶ እኔው በምሄድበት አውሮፕላን ከፊት ተቀምጦ ሲሄድ አየሁ። “አይ አማራ ምስኪኑ!” ይላል ዘመድኩን።

የአውሮፕላን ማረፊያውን ስያሜ ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ወያኔ ቁምጣውን ገልቦ ቅዘኑን በአማራው ላይ እንደተጸዳዳበት ዐይነት ስሜት ነው። ይቅርታ ለአገላለጹና ለቋንቋው።  እውነተኛውን ስሜት ለማሳየት በሚል ነው።   ዛሬም የአቢይ አህመድ  የአማራ  ማረጃ ቆንጨራ  የሆነው ሽመልስ  አብዲሳ አማራ ባረደ ቁጥር  ባሕር ዳር  እየሮጠ  ካባ  አልብሱኝ  ማለቱ  አልበቃው  ብሎ፣  ባሕር ዳር  ገብቶ  የብአዴን ስብሰባ ሲመራ  ውሏል።  የ ሽመልስ ጦር በዚያው ሰዐት በአንገር ጉተን እና ሌሎችም የወለጋ  ቀበሌዎች የተለመደውን የአማራ ጭፍጨፋ እያካሄደ በደም ጎርፍ እየዋኘ ያለበት ጊዜ ነው።  አማሮች በወለጋ የጅምላ መግደያ መጋዘኖች እየተዘጋጀላቸውና የጅምላ መቃብር እየተቆፈረላቸው ያለበት ወቅት ነው።  ከባሕር ዳር በመቶ ኪሎሜትር ርቀት በየጫካው የተበተኑ የወለጋ ተፈናቃዮች አባ ከና ያላቸው ሰው የለም።

በአቢይ ሕወሃት ጦርነት በቢሊዮን ብር በወደመው የአማራ ክልል እና በሚሊዮን አሃዝ ባለቀው የአማራ ልጅና ገበሬ እልቂትና ውድመት የሽመልስ ቡድን “ድል ተመዘገበ” እያለ ቦላሌውን ገልቦ ሲቀዝንበት ውሏል። በብአዴን ላይ። ብአዴን ደግሞ በአማራ ስም ስለሚንቀሳቀስ የተዋረደው በእጅ አዙር ማን እንደሆነ ግልጽ ነው። አዎ ድል አስመዝግበዋል። ሀገር አፍራሾቹ ከፍርሻ አጀንዳቸው አኳያ። ያንን ውርደትና ውድመት ግን ተበዳዩን “ድሌ” ነው ብለህ ተቀበል ማለት በሰው ገበታ ላይ ከማስታወክ ይበልጥ ይቀፋል።

ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ይላሉ አበው። ጊዜ የሰጠው ድንጋይማ ምንኛ ይበረታ!

ታኅሣስ 27፣ 2015

አሁንገና ዓለማየሁ

 

1 Comment

Leave a Reply

Your email address will not be published.

321656071 707440284356657 8403008459300155190 n
Previous Story

ጉዳዩ፦ የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፣ ሰቲት ሁመራ እና ራያ ጉዳይ የፍትህ እና የማንነት ጥያቄ ነው።

Fake dinner
Next Story

በአዲስ አበባ ላይ ስለሚካሄደው የተረኞቹ እራት ማብላትና ..ማእድ መጋራት…ወዘተ የስልቀጣና ዘረፋ ስልቶች

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop