July 22, 2022
4 mins read

የኦህዴድ አመራር በአዲስ አበባ ጉዳይ ሚስጥራዊ ስብሰባ አድርጎ ውሳኔ ማስተላለፉ ተሰማ!!

Abiy Ahmed Liar
Abiy Ahmed Liarበጠቅላይ ሚኒስቴሩ መሪነት ከፍተኛ የኦህዴድ አመራር አባላት ሰሞኑን ሚስጥራዊ ስብሰባ አድርገው በአዲስ አበባ ጉዳይ ውሳኔ ማስተላለፋቸው ተሰማ፡፡
በስብሰባው ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት ሽመልስ አብዲሳ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ አቶ አዲሱ አረጋ፣ የፌደራል ኮሚሽነሩ ደምመላሽ ገ/ሚካኤል እና ሌሎች ተገኝተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ጉዳይ በ2010 ዓ.ም ለተከሰተው ለውጥ ምክንያት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ፣ ይህም ቢሆን ባለፉት አራት ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ ከከተማዋ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እስካሁን ማግኘት አልቻለም ብለው አማረዋል፡፡
ለዚህም ጥሩ ማሳያ ሰሞኑን የተካሄደው የኮንዶሚኒየም እጣ ነው ብለዋል፡፡ “እጣው ባይሰረዝ ኖሮ በኦሮሚያ ትልቅ ተቃውሞ ይነሳ እንደነበር እናውቃለን” ብለዋል።
እንደሚታወቀው፣ አብዛኛው የእጣው ተጠቃሚ ኦሮሞ መሆን ይገባዋል የሚል ቅስቀሳ ውስጥ ውስጡን እየተደረገ ይገኛል። እጣው የወጣ ዕለትም በአዲስ አበባ ዙሪያ ኦህዴድ/ኦነግ/ሸኔ ያደራጃቸው ቄሮዎች በመኪና ተጭነው ወደ ከተማዋ በተለያዩ አቅጣጫዎች እንዲገቡ ተደርጎ ነበር። ጭፈራቸውን የከተማው ህዝብ በትዝብት ተመልክቶታል።
Addis Aba condoበመጭው ዓመት በከተማዋ ባሉ ትምህርት ቤቶች የኦሮሚያ ክልል መዝሙርና ባንዲራ ያለምንም ችግር እንዲሰቀልና እንዲዘመር የተቀናጀ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት፣ በኢኮኖሚው ዘርፍ ባለሀብቶችን መፍጠር እንደሚያስፈልግ፣ የኢኮኖሚውን በላይነት ሳይያዝ አዲስ አበባን መቆጣጠር እንደማይቻል አመራሮቹ አፅንኦት ሰጥተውታል፡፡
ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሚያ ክልል በከተማዋ ውስጥ ያለውን የአስተዳደር፣ የፖለቲካ እና ማህበራዊ ቁመና ለማሳደግ እስካሁን የተሰራው በቂ አይደለም ብለው አማረዋል፡፡
በጥቅሉ፣ ተሰብሳቢዎቹ አዲስ አበባን የኦሮሚያ አካል የማድረግ እንቅስቃሴው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጠው መለያየታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዘገባው—- ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ

https://twitter.com/ZemenuYA/status/1550607740179038211?s=20&t=wpjfcnFQXOKTsprMyXEIsQ

የመወደድ ርሃብ
የመወደድ ጥማት
ከአፋፉ ላይ ገፍቶ
ያቺን አገር ናጣት
ሁሉ ስለራሱ
ሁሌ እየመሰለው
መስታወት ፊት ቆሞ
ሌላ ‘ማይታየው
ወይ በስደት ቢሆን
ወይም በጦርነት
አልያም በችግር
በአፈና ባርነት
በነዚህ ሁሉ ውስጥ
መልኩ ‘ሚያስጨንቀው
የራስ ምስል ባርያ
ምንገዴው ሰው ማነው?!

Anania Sorri

294776517 5212818865482024 3224230989169398453 n

 

1 Comment

  1. እንደዚህ ዓይነት ዘገባ ከዋናው ባልደራስ ከአዲስ አበባ በመግለጫ መልክ ቢውጣ የተሻለ ነው። የተቃዋሚ/ተፎካካሪ ፓርቲ ሥራውም ነው። ዉሸት ከሆነም ተጠያቂነት ይኖራል። ‘ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ’ ግን ከአድማስ ባሻገር ስለሚገኝ ተጠያቂነትም ስሌለበት የፈለገውን “ዜና’ ቢዘግብ ተዓማኒነቱ በጣም ያነሰ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

295386938 5785578458141869 6000024880488984253 n
Previous Story

በግብፅ፣ በሱዳን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ትብብር ማስፋት የታላቁ ህዳሴ ጉዳይን ለመፍታት ያስችላል ሲሉ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ተናገሩ

8757638140156407629
Next Story

የአገርና የመንግሥት ሦስቱ ሥላሴዎች (National trinity) – አገሬ አዲስ   

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop