የኦህዴድ አመራር በአዲስ አበባ ጉዳይ ሚስጥራዊ ስብሰባ አድርጎ ውሳኔ ማስተላለፉ ተሰማ!!

በጠቅላይ ሚኒስቴሩ መሪነት ከፍተኛ የኦህዴድ አመራር አባላት ሰሞኑን ሚስጥራዊ ስብሰባ አድርገው በአዲስ አበባ ጉዳይ ውሳኔ ማስተላለፋቸው ተሰማ፡፡
በስብሰባው ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት ሽመልስ አብዲሳ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ አቶ አዲሱ አረጋ፣ የፌደራል ኮሚሽነሩ ደምመላሽ ገ/ሚካኤል እና ሌሎች ተገኝተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ጉዳይ በ2010 ዓ.ም ለተከሰተው ለውጥ ምክንያት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ፣ ይህም ቢሆን ባለፉት አራት ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ ከከተማዋ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እስካሁን ማግኘት አልቻለም ብለው አማረዋል፡፡
ለዚህም ጥሩ ማሳያ ሰሞኑን የተካሄደው የኮንዶሚኒየም እጣ ነው ብለዋል፡፡ “እጣው ባይሰረዝ ኖሮ በኦሮሚያ ትልቅ ተቃውሞ ይነሳ እንደነበር እናውቃለን” ብለዋል።
እንደሚታወቀው፣ አብዛኛው የእጣው ተጠቃሚ ኦሮሞ መሆን ይገባዋል የሚል ቅስቀሳ ውስጥ ውስጡን እየተደረገ ይገኛል። እጣው የወጣ ዕለትም በአዲስ አበባ ዙሪያ ኦህዴድ/ኦነግ/ሸኔ ያደራጃቸው ቄሮዎች በመኪና ተጭነው ወደ ከተማዋ በተለያዩ አቅጣጫዎች እንዲገቡ ተደርጎ ነበር። ጭፈራቸውን የከተማው ህዝብ በትዝብት ተመልክቶታል።
በመጭው ዓመት በከተማዋ ባሉ ትምህርት ቤቶች የኦሮሚያ ክልል መዝሙርና ባንዲራ ያለምንም ችግር እንዲሰቀልና እንዲዘመር የተቀናጀ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት፣ በኢኮኖሚው ዘርፍ ባለሀብቶችን መፍጠር እንደሚያስፈልግ፣ የኢኮኖሚውን በላይነት ሳይያዝ አዲስ አበባን መቆጣጠር እንደማይቻል አመራሮቹ አፅንኦት ሰጥተውታል፡፡
ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሚያ ክልል በከተማዋ ውስጥ ያለውን የአስተዳደር፣ የፖለቲካ እና ማህበራዊ ቁመና ለማሳደግ እስካሁን የተሰራው በቂ አይደለም ብለው አማረዋል፡፡
በጥቅሉ፣ ተሰብሳቢዎቹ አዲስ አበባን የኦሮሚያ አካል የማድረግ እንቅስቃሴው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጠው መለያየታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዘገባው—- ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ

የመወደድ ርሃብ
የመወደድ ጥማት
ከአፋፉ ላይ ገፍቶ
ያቺን አገር ናጣት
ሁሉ ስለራሱ
ሁሌ እየመሰለው
መስታወት ፊት ቆሞ
ሌላ ‘ማይታየው
ወይ በስደት ቢሆን
ወይም በጦርነት
አልያም በችግር
በአፈና ባርነት
በነዚህ ሁሉ ውስጥ
መልኩ ‘ሚያስጨንቀው
የራስ ምስል ባርያ
ምንገዴው ሰው ማነው?!

Anania Sorri

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ብልግናዎች: ፍላጎታችሁ ምን ይሆን?

1 Comment

  1. እንደዚህ ዓይነት ዘገባ ከዋናው ባልደራስ ከአዲስ አበባ በመግለጫ መልክ ቢውጣ የተሻለ ነው። የተቃዋሚ/ተፎካካሪ ፓርቲ ሥራውም ነው። ዉሸት ከሆነም ተጠያቂነት ይኖራል። ‘ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ’ ግን ከአድማስ ባሻገር ስለሚገኝ ተጠያቂነትም ስሌለበት የፈለገውን “ዜና’ ቢዘግብ ተዓማኒነቱ በጣም ያነሰ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share