June 29, 2022
3 mins read

‘‘እናቴ ሀገሬ በጠና ታመሻል፤ እግዚአብሔር ይማርሽ!!’’

Cry Ethiopia 1እያመመው መጣ… …!!

ከሰሞኑን ከያኒ ቴዎድሮስ ካሣሁን/ቴዲ አፍሮ ‘‘ናዕት – እያመመው መጣ!’’ በሚል ለሕዝብ ያደረሰውን ዜማ ሳዳምጥ፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንት ዘንድ ‘‘ደረቅ ሐዲስን ተናጋሪ’’ ተብሎ የሚጠራውና ከዐበይት ነቢያት ዘንድ የሚመደበው፣ የነቢዩ ኢሳይያስ የመጽሐፍ ቃል ወደ አእምሮዬ መጣ፡፡ እንዲህ ይነበባል፤

‘‘…  ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል፤ ከእግር ጫማ አንስቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም፤ ቍስልና እበጥ የሚመግልም ነው፤  አልፈረጠም፥ አልተጠገነም፥  በዘይትም አልለዘበም፡፡  … ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል፡፡  ደግሞስ ዓመፃን እየጨመራችሁ ለምን ገና ትቀሰፋላችሁ?!…’’  (ኢሳ. ፩፤፭-፮)

በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ ‘‘የእናቴ ልጅ’’ በመባል የሚጠሩት ሰባኪ ወንጌል፣ ቀሲስ መንግሥቱ- ስለ እናት ሀገር ኢትዮጵያ አብዛኛውን ጊዜ ከአፋቸው የማትጠፋና ያለንበትን ከባድ ጊዜ በደንብ የምትገልጽ አንዲት ስንኝ አለቻቸው፡፡ ይህች የቀሲስ መንግሥቱ ስንኝ የወቅቱን የሀገራችንን የመከራ ዶፍ፣ የሕዝባችንን ሰቆቃ፣ ሞት፣ ስደትና መፈናቀል- በአጠቃላይ የኢትዮጵያችንን ብርቱ ሕመም፣ ጭንቅ የምትገልጽ ናትና፣ አካፍላችሁ ዘንድ ወደድኹ፤

እናት ሀገር ታማ፣ ተኝታ በአልጋ ላይ፣

አምላኬ አትግደለኝ፣ ሞት ሽረቷን ሳላይ፡፡

እንደ መውጫም፤ አንጋፋው ፖለቲከኛ ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ፣ በተማሪነታቸው ዘመን (በ1959 ዓ.ም.) በቀድሞ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲተ ኮሌጅ/የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ‘‘የኮሌጆች ቀን’’ በዓል ካቀረቡት ግጥም ውስጥ- የሀገራችንን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጽ ስንኝ ለስንብት ይኾነን ዘንድ ላጋራችኁ ወደድኹ፤ እነሆ ስንኟ፤

‘‘… ይኼው ትታያለች ለሕዝብ በይፋ፣

ጥቁር ተከናንባ ጥቁር ተጐናጽፋ፡፡

እኔስ መስሎኝ ነበር ዘመድ የሞተባት፣

የእናት ሞት የአባት ሞት፣

የልጅ ሞት ያጠቃት፣

ለካ እሷስ ኖራለች ዘመን የሞተባት፡፡’’

(ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ/1959 ዓ.ም.)

‘‘እናቴ ሀገሬ በጠና ታመሻል፤ እግዚአብሔር ይማርሽ!!’’ (‘‘የእናቴ ልጅ’’የቀሲስ መንግሥቱ ምርቃትና ብሒል ናት)

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop