Hiber Radio: – ኢህአዴግ ለመለወጥ ያልተዘጋጀ ፓርቲ ነው ሲሉ ወ\ት ብርቱካን ሜድቅሳ ወቀሱ

/
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ መጋቢት 22 ቀን 2005 ፕሮግራም
<<…ፓርላማ መግባቴ ተገቢ እንደነበር አውቄያለሁ ።ፓርላማ በመግባቴ ነው እዛ ውስጥ መናገር የቻልኩት ።በዚያ መድረክ ተቃዋሚዎች ያለንን ሀሳብ ለማቅረብ እሞክራለሁ።…ተቃዋሚዎች የሚገባቸውን ያህል አያደርጉም የተባለው እኛ የምንችለውን ያህል እያደረግን ነው።ከዚህ በላይ ሰው መጠበቁ ክፋት የለውም ።ተቃዋሚዎች የሚችሉትን ያህል እያደረጉ ነው።ከዚህ በላይ መደረግ አለበት የሚል የሌላውን ባላውቅም አንድነት ውስጥ ገብቶ ማድረግ ይችላል …>> የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ብቸኛው የተቃዋሚ የፓርላማ አባል ከሰጡን ቃለ ምልልስ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)
የቬጋስ የሁለቱ ታላላቅ ኩባንያ የታክሲ ሹፌሮች የስራ ማቆም አድማ አስተባባሪዎች ከሰጡን ቃለ መጠይቅ (ያዳምጡት)
<<ዳላስ ላይ ከዛሬ ሶስት ዓመት በፊት ኢትዮጵያውያን የታክሲ አሽከርካሪዎች ያደረጉት የስራ ማቆም አድማ የከሸፈው አንዱ ሲያቆም ሌላው እየተደበቀ እየሰራ ነው። ሁሉም ስላልተባበረ አልተሳካም። በፍ/ቤት ግን ውጤት አግኝተናል …>> አቶ ሙሉዓለም ተክሉ የቀድሞ የዳላስ የስራ ማቆም አድማ አስተባባሪዎቹ አንዱ ለህብር እንደተናገሩት
ተጨማሪ ቃለ ምልልስ አለን
ዜናዎቻችን
– በቬጋስ አንድ የታክሲ ሾፌር የስራ ማቆም አድማ በሰዓታት ውስጥ ወድቆ ህይወቱ አለፈ
* የስራ ማቆም አድማውን የፍሪያስ አሽከርካሪዎች ተቀላቀሉ
– አንድነት በአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ በአገዛዙ እየተፈጸመ ያለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት አወገዘ
– ኢንጂነር ሀይሉ ሻውል በብሄረሰቡ አባላት ላይ የሚፈጸመው ግፍ የዘር ማጥፋት ወንጀል መሆኑን ገልጸዋል
– ኢህአዴግ ለመለወጥ ያልተዘጋጀ ፓርቲ ነው ሲሉ ወት ብርቱካን ሜድቅሳ ወቀሱ
– ወሮ አዜብ መስፍን “ባለቤቴ መለስ የግል አካውንት የመንጃ ፈቃድ አልነበረውም “ሲሉ ተናገሩ አባባላቸው አገራሞት ጭሯል
* ብዛት ያለው ወርቅ ከደሱዳን ወደ ኢትዮጵያ በህገወጥ መንገድ ይገባል ተባለ፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  ወለምታ እና የጡንቻ መሸማቀቅ ሲደርስ መደረግ የሚገባቸው ነጥቦች

1 Comment

Comments are closed.

Share