የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ “የረዳት አብራሪው አኩሪ ገድል የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃ እስኪወጣ ይቀጥላል” አለ

“የወጣት ሃይለመድህን አበራ አኩሪ ገድል የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነትእውን እስኪሆን ድረስ ይቀጥላል” ሲል የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ። ንቅናቄው ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ ለአለም ህብረተሰብ ያስተጋባው መልዕክት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ድምፅን ነውና፤ አላማና ተግባሩም የሁሉም ኢትዮጵያዊ ምኞትና ፍላጎት መሆኑን በፅኑ ያምናል” ብሏል። በተጫምሪም አኩሪ ተግባር ፈጽሟል ላለው ለረዳት አብራሪው የንቅናቄው የክብር አባል እንዲሆን የምስክር ወረቀት ሰጥቷል፡፡ ሙሉ መግለጫው ከምስክር ወረቀቱ በታች እንደወረደ እንደሚከተለው ተስተናግዷል።

“የወያኔ/ኢህአዴግ ጨቋኝ ሥርዓት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ቁጥር ስፍር የሌላቸው አፋኝ ህጎችን በመጫን፤ እንዳሻው ንጹሃን ዜጎችን መጥፎ ስም በመስጠት፤ ባልሰሩት ሃጥያትና በተፈበረከ የሃሰት ወያኔያዊ ውንጀላ በየእስር ቤቱ እንዲማቅቁ እያደረገ መሆኑ ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግልጽ ነው። ይህ አፋኝ ሥርዓት የምንወዳት ሃገራችን ኢትዮጵያንና ህዝቧን የማጥፋት እኩይ አላማ ሰንቆ፤ ምሁራን ዜጎች ለሚወዷት ሃገራቸውና ለሚሳሱለት ህዝባቸው የበኩላቸውን ማበርከት እንዳይችሉ፤ በተለይ ወጣት ምሁራን በሃገራቸው ጉዳይ ላይ ቀጥተኛ ተሳተፊ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ግድያ፣ እንግልት፣ ጭቆና፣ በደልና፣ ወከባ እያደረገ ይገኛል።

ይህ ፋሽስት ሥርዓት በዘረጋው አፋኝ መዋቅር ህዝብ እርስ በርሱ በጥርጣሬ እንዲኖር፤ ቤተሰብ ከቤተሰብ እንዳይተማመን፤ አንዱ ብሄር በሌላው ብሄር ላይ ጥላቻ እንዲኖረውና፤ አንዱ ሃይማኖት ከሌላው ሃይማኖት ጋር በፍቅር፣ በመተሳሰብና፣ በመቻቻል እንዳይኖር፤ ባጠቃላይ በሃገሪቷ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር፤ ብሎም ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ከምድረገጽ ፈፅሞ ለማጥፋት፤ ያልፈነቀለው ድንጋይ ባይኖርም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ያስተሳሰረው የፍቅርና አብሮ የመኖር አኩሪ ባህሉ ነውና፤ የወያኔ/ኢህአዴግ እልቆ መሳፍርት መሰሪ ተንኮልና ደባ ሳያንበረክከው፤ ሥርዓቱ በወጠነው መንገድ ሳይሆን በፍቅር፣ በመተሳሰብና፣ በመቻቻል አንድነቱን ጠብቆ አሁን ድረስ መዝለቅ ችሏል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በዋሽንግተን ዲሲ የሽግግር ምክርቤቱ አመራርm ስብሰባ

የታፈነ ጭስ መውጫ አያጣም ነውና፤ ታጋሽና ሰላም ወዳድ የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆናውና በደሉ ከልክ በላይ ስለሆነበት፤ እየደረሰበት የሚገኘውን ቅጥ ያጣ ግፍ በተለያዩ አያሌ መንገዶች ሲገልጽ ቆይቷል። በየካቲት 10, 2006 የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪ በሆነው ወጣት ሃይለመድህን አበራ የተፈጸመው አኩሪ ተግባር ይህንኑ የስርዓቱን አስከፊ ገጽታና በህዝብ ላይ የሚደርሰዉን ግፍ፣ ወከባ፣ እንግልት፣ እስራት፣ ግድያና፣ ሰቆቃ የሚያረጋግጥ አይነተኛ ክስተት ነው። ወጣት ሃይለመድህን አበራ በሥርዓቱ እየደረሰበት የነበረዉን አስከፊ በደል ለማምለጥ በግሉ በርካታ መንገዶች ነበሩት። የአውሮፕላን አብራሪ በመሆኑ አለም ላይ ካሉ ሃገራት ሁሉ በሚፈልግበት የመሄድና የመኖር እድሉ በእጁ ነበር። በኢኮኖሚም ቢሆን በሃገሪቱ ከፍተኛ ክፍያ ከሚያገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች አንዱ በመሆኑ በግል ኑሮው ተንደላቆ የመኖር ችሎታው እንደነበረው ለማንም አጠራጣሪ አይሆንም።

ነገር ግን ወጣት ሃይለመድህን አበራ የኢትዮጵያ ህዝብ ቁስል ስላመመው፤ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚደርሰው ግፍና በደል የሱም እንደሆነ ቀድሞ ስለተረዳ፤ ህልሙ የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት እውን ሆኖ፤ መብቱ ተከብሮለት፤ በሃገሩ የመኖር ተስፋን አንግቦ፤ በፍቅር፣ በሰላምና፣ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ሲኖር ማየት በመሆኑ፤ በዙሪያው የጨበጠው እድል ሳያጓጓውና ወጣትነት ሳያታልለው፤ በማስተዋል ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት እጅግ ከፍተኛ መሥዕዋትነትንና ጀግንነትን በተግባር ፈጽሟል።

የወጣት ሃይለመድህን አበራ ታላቅ ተግባር የወያኔ/ኢህአዴግ ከልክ ያለፈ ግፍንና የኢትዮጵያ ህዝብን የታፈነ ሰቆቃ ለአለም ህዝብ በይፋ ከማጋለጡም ባለፈ፤ በኢትዮጲያችን እጅግ ብዙ እሱን መሰል ጀግና ወጣቶች ያለጥርጥር እንደሚገኙና፤ በኢትዮጵያ ነፃነት፣ ፍትህና፣ እኩልነት በአስተማማኝ ሁኔታ እውን እስኪሆን ድረስ፤ ህዝብ ለነፃነቱ ምንግዜም እንደማይተኛ ያረጋገጠ ብሄራዊ የጀግንነት ተግባር ነው። በመሆኑም ወጣት ሃይለመድህን አበራ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት የፈፀመው አኩሪ ተግባርና የከፈለው ታላቅ መሥዕዋትነት በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ለዘላለም ሲታወስ እንደሚኖር ጥርጥር የለንም። ነገር ግን በዚህ ውድ ኢትዮጵያዊ ጀግና የተከፈለው ታላቅ መሥዕዋትነት በኢትዮጵያ ሰላም፣ ፍትህ፣ እኩልነትና፣ ተስፋ እንዲመጣ በቁርጠኝነት የታቀደ በመሆኑ፤ ውጥኑ ለታለመለት አላማ ግቡን እንዲመታ፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ እድሜ፣ ሃይማኖት፣ ብሄር፣ ወይንም ሌላ ማንኛውም ልዩነቱ ሳይገድበው፤ ለጋራ ነፃነቱ በጋራ በመነሳት አንድነቱን ለአለም ማሳየትና የዚህን ቆራጥ ኢትዮጵያዊ ጀግንነት ማስተጋባት ይኖርበታል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለአፋኙ ብልጽግና ጊዜው መሽቷል ከአማራ ጋር እንቁም | Hiber Radio

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ ወጣት ሃይለመድህን አበራ ለአለም ህብረተሰብ ያስተጋባው መልዕክት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ድምፅን ነውና፤ አላማና ተግባሩም የሁሉም ኢትዮጵያዊ ምኞትና ፍላጎት መሆኑን በፅኑ ያምናል። ስለሆነም ንቅናቄያችን በአለም ዙሪያ የሚገኙ አባላቶቹን ሙሉ በሙሉ በማስተባበር፤ የወጣት ሃይለመድህን አበራን ድምፅ መልሶ በማስተጋባት፤ አንድነቱን ለአለማቀፉ ህብረተሰብና ለአለም መንግስታት፣ እንዲሁም ለሚመለከታቸው አለማቀፋዊ ተቋማት በሙሉ በማስመስከር፤ እውነታዉን ለማሳወቅ የተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎችን፣ ዲፕሎማሲያዊ ሂደቶችንና፣ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን በማከናወን፤ ግንባር ቀደም ሚና እንደሚጫወት ከወዲሁ እያስታወቀ፤ ወጣት ሃይለመድህን አበራ ለኢትዮጵያውያን የነፃነት ትግል ላበረከተው ታላቅ አስተዋዕፅዎ ብሄራዊ ጀግና ሲል መሰየሙን ለኢትዮጵያ ህዝብ በታላቅ ኩራት እያበሰረ፤ የብሄራዊ ጀግና የክብር የምስክር ወረቀት በአድናቆት ያበረክታል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ በዚህ ዘረኛ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ከልክ ያለፈ ጭቆና፣ ረገጣና፣ እንግልት ሠለባ ሆኖ በመሰቃየት ላይ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ህዝብ ተቆርቋሪ ለሆናችሁና በምንወዳት ሃገራችን ሰላም፣ ነፃነት፣ ፍትህ፣ ተስፋ እንዲሰፍንና ለህዝብ የሚበጅ ቀና ለውጥ ለዘለቄታው ይሰፍን ዘንድ ለምትመኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ፤ እንዲሁም ለተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ለሃይማኖት ተቋማትና፣ ለሲቪክ ማህበራት ታላቅ ሃገራዊ ሃላፊነትና የህዝብ አደራ በጫንቃችሁ እንደተሸከማችሁ በመገንዘብ፤ ልዩነታችሁን ወደ ጎን በመተው ለዚህ ወሳኝ ህዝባዊ ጥሪ በአንድነት ምላሽ በመስጠት የሚጠበቅባችሁን ህዝባዊ አደራ እንድትወጡ ዘንድ በጥብቅ እያሳሰበ፤ ሃገራዊ የመተባበር ጥሪውን በአክብሮት ያቀርባል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ

8 Comments

  1. Really? You guys really mean this? You are officially endorsing terrorism. His persumed causes could be right but his actions by no means can be right. This to extreme.

    Sorry I don’t agree. Zehabesha you should have not be posted. This kind of endorsement will encourage other groups.

    Do you think democracy will come through violence? I don’t think so.

    • Yes, defensive violence can facilitate democracy. Apparently, you have not read World or American history. Before democracy came into being, general Washington had to fight a bitter war with British colony. The civil war was fought to incorporate African American in to democracy. Democracy swept Europe after the French revolution. However, which violence are you talking about here? How many people have died in this particular case? Zero, none, nada, nil. Apparently, you have a strange understanding of violence and terrorism just like the blind supporters of the illegal tplf regime. You started to lose after the demise of your terrorist champion. From here on, it is going to go down hill. Nothing can changes that.

      • Honestly I have not read Amerian history, I promise I will read. But regarding French I think you have not read the whole story about the revolution. That revolution has removed one brutal king and end up putting in power another brutal king, who? Napoleon.

        Even our recent history shows us the same. The student movement removed the king and who came to power hahahaha Mengistu and wait for it who removed Mengistu the youth of Tigiry under pretext of democracy who came to power wow Meles the founder of this regime which you guys are planning to remove under pretext of democracy.

        If you think you value democracy and think your are independent you would not have said this. You would have known that violence or development alone won’t bring change or democracy.

    • What is meant by violence ? What terrorism have you heard of recently, even regarding the co -pilot? Don’t confuse yourself not to be confused.

  2. Hey hey hey

    Excuse you…… haven’t you heard that hijacking is a terrorist act for its all purposes and intents. Bro I am neither supporter or hater of any of you people ( da government or opposition). You both are wrong the present politics of Ethiopia is messed up between three hateful groups the people like you so called one ethiopia group with hidden agenda, the arrogant group of tplf and last but not least the narrow minded oromos. For sure you will fall in one of these three especially the first one.

    Eat your heart bro if you think you have some heroism left in you, you will not be posting this kind of nonsense, you would have acted like one…..

    Whatever you say it is hijacking, out dated, violence and I don’t support. You can believe whatever you want or interpret the way you like it for me it is and what it look like are the same.

  3. Enante min aynet maferiyawoch machihu? Awroplan metilef keto bemin ayinet temama melekia bitilekut yihon “gedil” yemihonew? Mengistin meqawom lela yehagerin wud nibiretina ye’ayer mengedun melkam getsita maqoshesh lela. A’emirow tenegnam yihun nik ye’redat abrariwun dirgit hulem bihon betsinu eqawemewalehu!!!! Ethiopia Lezele’alem Tinur!!!!!

  4. to biniyam tezera
    egig betam mafriya kinchib hasab yaleh ante ena endante ayntu kadrie ehadig new. terrorist beleh yewonkew terrist yemilewun ke woyanie ehadig yewosedkew defination engy zemenawiw jegna yetlef yalewun yenanten bezer yetetlflfe poletica serat le alem masayet new. degmo asaktual. eskmechie new endezih sewun afnachuh yemtmeru? yih hala ker hasab ahun ayaktmlte new.
    we ethiopian need a change!!!!

Comments are closed.

Share