February 21, 2022
5 mins read

የኢትዮጵያ ሰማይ! –ፊልጶስ

ትላንት ያለንበርኩኝ፣ ነገም የማልኖር
ከቃንቄ ብርሃን፣ ከነቁጥ ያነስኩ ፍጡር
የማለዳ ጤዜ፣ ለዚች ዓለም-ምድር፤

መነሻ-መድረሻው፣ ሚስጢር ቢሆንብኝ
ልጥይቅህ ደፈርኩ ግራው ቢገባኝ።

በአርባ አራቱ ታቦት
በቅዱስ ሰማዕታት፤
በምስኪኗ እናት- በቆዘመው አባት
በወላጅ አልባዎቹ- በእነዚያ ህጻናት
በተደፈሩት፣ በተዋረዱት
በፈሰሰው ደም፣ መሰዋት በሆኑት ፤

በአንጋጠጡ ዓይኖች
በተዘረጉ እጆች፣
በአዘኑ ልቦች፤

በስደተኞቹ
በባይታወረሮቹ፤

በረሃ-ውቅያኖስ፣ በልቶ ባስቀራቸው
በምንዱባኖቹ፣ ድምጽ በሌላቸው
በሚቅበዘበዙ ቀን ጨልሞባቸው፤—

ልማጸንህና!
ልለምንህና!

የኢትዮጵያ ሰማይ!
“እህ” ብለህ ስማኝ
ልጠይቅህና፣ እስቲ መልስ ስጠኝ
እናታለም ምድሬን!—-
አገሪን! ወገኔን! ከቶ ምን ነካብኝ???–

አንተ ክላይ ያለህ፣ የኢትዮጵያ ሰማይ
ምን ትታዘባለህ አቆልቁለህ ስታይ?

አሃዱ ዓለም ተብሎ፣ ቀደምተ-ፍጥረት
ኢትዮጵያ ስትባል የገነት “አፍላጋት”
ዛሬ እንዴት ሰው ያምናል፣ ጥንት ለሚያውቃት?—–

ከላይ ሆነህ አንተ፣ ከታች ሆነን እኛ
ምን ብለህ ታዘብክ ፣ ስንሆን መናኛ፣ ስንሆን ምፃ’ተኛ።

ተርፎ ከሚደፋው፣ የዕለት ጉርስ አ’ተን
እንላብሰው ልብሳችን፣ አልቆ ከላያችን፣
ተጋልጦ ገላችን፤

እምቦቀቅላ ልጅ፣ የሙት እናት ጡት
ሩሄ ሆኖበት ሊጠባ ሲጎትት፤

ነፍሰ ጡሯ “አምሳለ ፍቁር”፤ ሆዷ ሲተለተል፤ ጽንሷ ሲገደል
በልጇ ሬሳ ላይ ስታለቅስ ሃርሞ ፣ ”ዋቆ የት ነህ?”ስትል፤

የመከራው ቋቱ ፣ የሰቆቃው ጽዋ ፣ የታሪክ ማኅደሩ
ትውልድ አልፎ- ትውልድ፣ ላይማር- መማሩ፤

ወገን- በወገኑ፣ ሰይጣን የማያውቀው፣ ይኽ ሁሉ ስቃይ
ከቶ ምን ይመስላል ከላይ ሆኖ ሲታይ?

ነገራችን ሁሉ እንዳይሆን !
እንዳይሆን! እንዳይሆን!………
“—-ከፈርሱ ጋሪን እንስቀድማለን፤

አሳን ለገደል – ዝንጀሮን ለባህር
እናሰማራለን፤
አንበሳን ለሸክም – በቅሎን ለቀንበር
እርሻ እንልካለን፤
ብረት ምጣድ ጥደን፣ ቅቤ እንጋግራለን።—-”
ይኽ ሁሉ ድንብርብር፣ ከቶ በአንተ ሰማይ እንደምን ይታያል?
ይኽን ያህል ዘመን ምንስ ታዝበሃል?–
ለስልጣኔ አቻ፣ ድንቁርናን ወርሰን
ከነበረን ዕምነት እርሾውን አድርቀን፤
የእፍኝት ልጆች፣ ከብረው ሲነግሱብን
እውነት አንገት ደፈታ፣ ሃሰት ሲገንብን፤
‘ርስ – በእርስ ተባልተን ስንተላለቅ
ሰማይ ያንተ ዝናብ፣ ምንጩ ለእኛ ሲደርቅ
አገር አልባ ስንሆን፣ ዓለም ሲመጻደቅ፤
አንተ የሁላችን፣ የጋራ የሆንከው
አንጋጠን ስናይህ፣ በእውነት አለወይ ለ’ኛ የደበከው?—–
——ግን እኔ የምልህ የኢትዮጵያ ሰማይ……፡
ቢጨንቀኝ እኮ ነው!
ቢጠባኝ እኮ ነው!
መላው ቢጠፋብኝ
እድሜዩን በሙሉ ሚስጥሩ ቢሆንብኝ
የልቤ-ደም እምባ፣ ዓይኔን ቢያስጓጥጥኝ፤
በድቅድቅ ጨለማ፣ በጋግርታም ለሊት ዓለም “በተኛበት ”
እኔና ወገኔ እንቅልፍ ባጣንበት
የመከራው ዝናብ፣ ዶፍ በሚወርድበት፤
አንተን ማናገሩ፣ ይቅርብኝ ልተወው
ሰማይን ለሚያክል ጥያቄ አቅርቦ መልስ ያገኘ ማነው::
ግን እኔ የምልህ !– የ’ኔን ዘንጋውና
አንተ የሚሳንህ ምንም የለምና
አዎ—–የኛ ነገር …….
ብንለው! ብንለው !ብንለው! ብንለው!
አንስተን -ብንጥለው፣ ጥለን – ብናነሳው፤
ውሃ መውቀጥ ሆኖ፣ ውሉ ጠፍቶብናል
ከሰው ተራ ወርደን፣ ስብዕናችን ጠፍቷል።
ስለዚህም ሰማይ—–
ፍቃድህ ከሆነ፣ ከፈቀድክልን
በቃችሁ ብለህ ኢትዮጵያን አጽናልን
ወይም ምድሯን ውረስ፣ አንተ ተተካለን።

——//——ፊልጶስ
e-mail: philiposmw@gmail.com

Leave a Reply

Your email address will not be published.

274439035 694441458677302 5621477647791217402 n
Previous Story

በእብደት ላይ እብደት እየጨመሩ ያሉት የአድዋ ልሂቆች – ነጋሪት

274463310 249396784050451 5288271212268270033 n
Next Story

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት አጽድቋል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop