ተጠየቅ (ዘ-ጌርሣም)

ተጠየቅ በህግ ፊት
ለፈፀምከው ክህደት
ቁምና ተሟገት
ሳይበየንብህ የዕድሜ ልክ እሥራት
ምስክር ከሌለህ
ዋቢም ካልቆመልህ
በወፍና ድንጋይ
ቀርበህ አደባባይ
እሰጥ አገባ በል
ከቻልክም አስተባብል
መሃላውን ፈፅም እውነቱን ተናገር
ህሊናህን ሞግት ያለ መደናገር
ተጠየቅ በህግ ፊት
ለፈፀምከው ክህደት
ቁምና ተሟገት
ሳይበየንብህ የዕድሜ ልክ እሥራት
ትናንት ሕዝብ በደልክ
የሀገር ጦር በተንክ
ከሥራም አባረርክ
ከሀገር አሰደድክ
የተፋለመህን እሥር ቤት ውስጥ አጎርክ
በጭካኔ በትር አካላት አጎደልክ
ወጣት አኮላሸህ
ጉብሏን አመከንህ
የእምነት ስዎች ደፍርክ
ሃይማኖት አረከስክ
ታሪክን
እምነትን
ባህልን
ሰብዕናን (ሰውነትን)
አቆሸሽክ
ተጠየቅ በህግ ፊት
ለፈፀምከው ክህደት
ቁምና ተሟገት
ሳይበየንብህ የዕድሜ ልክ እሥራት
ገበሬ እያሞገስክ
እሱኑ የበደልክ
መልሰህ የገደልክ
አምኖህ የኖረውን
አብሮህ የበላውን
አብሮህ የሞተውን
በቸገረህ ጌዜ አብሮህ የቆመውን
ደክሞት በተኛበት
በደረቁ ሌሊት
መከላክያውን
የሀገር መከታውን
ብሔር የሌለውን
ፖለቲካ ስልጣን የማይመኘውን
የዚያችን ድኃ ልጅ
የዚያን አፈር ገፊ የገበሬን ቀኝ እጅ
አንተን እያኖረ ለራሱ የማይበጅ
ሲያገኝ ፍርፋሪ
ሲያጣ ጦም አዳሪ
እሱ እየሞተ ሌላውን አኗሪ
በሆነው ወገን ላይ
በፈፀምከው በደል ባደረስከው ስቃይ
የጥይት እሩምታ እንዳዘነብክበት
የእጅህን አታጣም ቀኗ የመጣችለት
ተጠየቅ በህግ ፊት
ለፈፀምከው ክህደት
ቁምና ተሟገት
ሳይበየንብህ የዕድሜ ልክ እሥራት

2020-11-19

ተጨማሪ ያንብቡ:  አቡኑ ጳጳሳት በእንጀራ ታነቁ!

1 Comment

  1. አማራ እና ወልቃይት ጠገዴዎች አትቸኩሉ ነፃ ወጣን ብላችሁ ፈታ ለማለት። አዲስ አበቤዎችም ከዛሬ ሶስት አመት በፊት ትህነግ/ወያኔ አዲስ አበባን ለቃ ስትወጣ አዲስ አበባ ነፃ ወጣች ብለው ፈታ ማለት ጀምሮዋቸው ነበር። እያደር ነው የባሰባቸው ተረኞች መተካታቸው እና ከእስር የተፈቱት እነ እስክንድርንም ጨምሮ ነፃ አለመውጣታቸውን ወልቃይት እና ራያም ለውጥ እንዳላዩ አዲስ አበቤ የተገለጸለት።

    ስለዚህ ነፃ ወጣን ለማለት አንቸኩል ገና ብዙ ብዙ አደጋዎች በተለይ አማራ ላይ በያለበት ከአዳማ ፣ ከባህር ዳር ፣ ወለጋ ፣ አዲስ አበባ ፣ ደቡብ ጉራ ፈረዳ ፣ዳያስፖራ ሳይቀር እንኳን በማንነታችን አማራ ላይ ሞት ዙርያችንን ተጋርጦብናል። ለምን ይመስላችሁዋል የኦሮሚያ ልዩ ኃይልንም አስታጥቀው ከአማራ ልዩ ኃይል አጠገብ እብረው ያላሰለፉት?

    አንዘናጋ!

    ሁሉም ለአንዱ ፡ እንዱም ለሁሉም!!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share