የኢሕአደግና የግንቦት ስባት ድርድር ? ግርማ ካሳ

የኢሕአደግና የግንቦት ስባት ድርድር ? ግርማ ካሳ
Muziky68@yahoo.com

ዲሴምበር 3 ቀን 2013 ዓ.ም

«የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት ለግንቦት ሰባት የእንደራደር ጥያቄ አቀረበ» ሲል ኢሳት ሰበር ዜና አሰማን። ዶር ብርሃኑ ነጋንም በማቅረብ በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ እንዲሰጡም አድርጓል። ምንም እንኳን የቀረበዉን ዘገባ ከሌላ ምንጭ ማጣራት ባይቻልም፣ ዜናዉ እዉነት ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ግን ይሰማኛል። አገዛዙ ከኦብነግ፣ ኦነግ ከመሳሰሉ ጋር ድርድር እየጀመረ፣ የማቋረጥ ልማድ እንዳለው ታሳቢ በማድረግ። የግንቦት ሰባት «እንደራደር» ጥያቄም ከዚያ የተለየ አይሆንም። በሳዊዲ

የድርድር ጥያቄዉን ይዘው የመጡ መልእክተኖች እነማን እንደሆኑ የተገለጸ ነገር የለም። ዶር ብርሃኑም «ጥያቄዉ የመጣዉ ከብዙ አቅጣጫዎች ነው» ከማለት ዉጭ ትንፍሽ ያሉት ነገር የለም። ከአንዳንድ የግንቦት ስባት አመራር አባላት ጋር የቅርብ የስራ ትውውቅ ባላቸውና፣ በቅርቡ ኢትዮጵያን በጉበኙት ፣ በተከበሩ አና ጎምዜ ይሆን መልእክቱ የመጣዉ ? ወይንስ ብዙ ጊዜ በሽምግልና ተግባር በመሰማራት በሚታወቁት በተከበሩ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳእቅ ? ወይስ በሃይማኖት አባቶች ? ወደፊት የምናውቀዉ ይሆናል።

ድርድር መቼም ቢሆን የሚደገፍ እንጂ የሚጠላ አይደለም። እርቅና ሰላም እንዲሰፍን፣ ኢትዮጵያዊያን ልዩነቶቻችንን በዉይይት እንድንፈታ የሚገልጹ በርካታ ጽሁፎችን አስነብቢያልሁ። ነገር ግን በኢትዮጵያ መልካም አስተዳደር ለማስፈንና የዲሞክራሲ ተቋማትን ለመገንባት ያስችል ዘንድ፣ ያለ አንዳች ቅደም ሁኔታ ለመነጋገር ፍቃደኛ ከሆኑ፣ አገር ዉጥ ካሉ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር፣ ኢሕአዴግ «በፍጹም አልደራደርም» እያለ፣ በሌላ በኩል «ጠመንጃ አንስተን እንታገላለን» ለሚሉ የድርድር ጥያቄ ማቅረቡ ግን ምን ይባላል ? በአንድ በኩል ብእር አንስተዉ በመጻፋቸው፣ «ከግንቦት ሰባት ጋር ተነጋግራቹሃል። ከሽብርተኞች ጋር አብራቹሃል» እየተባሉ፣ በዉሸት ክስ ዜጎች ለእድሜ ልክ እስራት እየተደረጉ፣ በሌላ በኩል ከ«ሽብርተኞቹ» ግንቦት ሰባቶች ጋር መነጋገር፣ ግብዝነትን አያሳይምን? አገዛዙ ሌላ አላማ ኖርት እንጂ በርግጥ ሰላም ፈልጎ ነዉ ማለት እንችላለን ?

ተጨማሪ ያንብቡ:  የደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ከድጡ ወደማጡ በትንሣኤው ዕለት - (የግል አስተያየት)

በነገራችን ላይ ኢሕአዴግ ድርድር የጠየቀው ግንቦት ሰባትን ፈርቶ እንዳልሆነ መታወቅ አለበት። በዚህ ላይ ብዙ አንሳሳት። ግንቦት ሰባትን ኢሕአዴግ አይፈራም። እስቲ ንገሩኝ ለምንድን ነዉ ኢሕአዴግ ግንቦት ሰባትን የሚፈራዉ? የድርድር ጥሪ መቅረቡ በምንም መስፈርትና መለኪያ የግንቦት ሰባት ጥንካሬንም አያሳይም። ጥንካሬ የሚለካው በፍሬና በዉጤት ነዉ። ጥንካሬ የሚለካው በሜዳ ነዉ። ጥንካሬ ኢሕአዴግ በሚያወራዉ አይለካም። በመሆኑም ግንቦት ሰባቶች «ኢሕአዴግ ድርድር ከኛ ጋር የፈለገዉ ፈርቶ ነዉ፤ ስላሰጋነው ነዉ፤ ጥንካሬያችንን አይቶ ነዉ፤ ወዘተረፈ» እያሉ ብዙ ዳንኪራ ባይመቱ ይሻላል። ሰዉ ይታዘባቸዋል። ይልቅስ እራሳቸዉን ቢመረምሩ ዉጤት በሚያመጡ እንቅስቃሴዎች ላይ ቢሰማሩ ይበጃል ባይ ነኝ። (በዚህ አርእስት ላይ፣ ይረዳቸው ዘንድ ፣ ለግንቦት ስባቶች የተጻፈ ምክር አዘልና አቅጣጫ ጠቋሚ ግልጽ ደብዳቤ በቅርብ ጊዜ አቀርባለሁ)

እንደሚመስለኝ ኢሕአዴጎች ለመደራደር ጥያቄ ያቀረቡት፣ የአለም አቀፍ ማህበረሰብን ግፊት ለመቀነስ ነዉ። አራት ነጥብ። ግንቦት ሰባት ከሻእቢያ ፍቃድ ዉጭ ሊደራደር እንደማይችል፣ ጥያቂያቸዉን ዉድቅ እንደሚያደርገዉ ከወዲሁ ያዉቃሉ። ነገር ግን «ይኸው እናንተ ከተቃዋሚዎች ጋር ተደራደሩ ስትሉን፣ እሺ ብለን፣ በራሳችን አነሳሽነት፣ ለግንቦት ሰባት፣ ኦብነግ ጥያቄ አቀረብን። እነርሱ ግን ፍቃደኛ አልሆኑም። ከኦብነግ ጋር ተደራደርን ፣ ግማሾቹ እሺህ ብለው የተወሰኑት ግን እምቢ አሉ። ታዲያ ምን አድርጉ ነዉ የምትሉን ? » ለማለት ነዉ።

አገር ቤት ያሉ ፓርቲዎችን «እንደራደር» ቢሉ እሺ እንደሚሉ፣ በዚያም ድርድር የፖለቲካ ምህዳሩን በትንሹም ቢሆን መክፈት ኢሕአዴጎች እንደሚኖርባቸው፣ የፖለቲካ ምህዳሩን በትንሹ ከከፈቱና በአንጻራዊነት ዴሞክራቲክ ምርጫ ከተደረገ፣ እንደሚሸነፉ ያውቃሉ። በመሆኑም ባለ አቅምና ጉልበት፣ ጠንካራ ፓርቲዎችን እያዳከሙ፣ ዋጋ ቢስና ምናምንቴ ዘጠና፣ መቶ የሚቆጠሩ ፓርቲዎችን አየለቃቀሙ፣ ዲሞክራሲ እንዳለ ለማስመሰል ይሞክራሉ። አገር ቤት ያሉት ጠንካራ መሪዎችን በአንድ በኩል እያሰሩና እያወኩ፣ ዉጭ ካሉ፣ ሊስማሙ ከማይችሉ ጋር እንደራደር በማለትም፣ የ«ሰላም አርበኞች» መስሎ ለመታየት ይጥራሉ። አሳዛኝ !!!!!
ድርድርና ሰላም የሚጠላ የለም። ኢሕአዴግ በቅንነት ለእርቅ ተዘጋጅቶ፣ እራሱን አሻሽሎ፣ የሕዝብን ጥያቄ ሰምቶ ፣ የዜጎችን መብትና ነጻነት አክብሮ፣ ለአገራችን ልማትና ብልጽግና ከሁላችንም ጋር በጋራ ለመስራት ቢዘጋጅ፣ ደስታዬ ገደብ አይኖረዉም። ያም እንዲሆን የድርሻዬን ከመወጣት ወደ ኋላ አልልም። ጸሎቴም ነዉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የግጭትና የጦርነት ሁሉ መነሻ ስግብግብነትና እራስ ወዳድነት ነው! (አገሬ አዲስ )

ነገር ግን ፣ ያ አልሆነም። ኢሕአዴግ ዉስጥ ያሉ ጥሩ ሰዎች እየተዋጡ፣ ከመጋረጃ ጀርባ የተቀመጡ፣ ጥቂት ፈላጭ ቆራጭ የሆኑ፣ አክራሪዎች ድርጅቱን ወደ ገደል እየከተቱት ነዉ። ምንም እንኳን በአቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራ የመንግስት መዋቅር ቢኖርም፣ አክራሪዎቹ የሚመሩት ሁለተኛና ሚስጥራዊ የመንግስት መዋቅር ያለ ይመስለኛል። በዚህ መዋቀር ያሉቱ የፈለጉትን ይገድላሉ። የፈለጉትን ለፍርድ ቤት ትእዛዝ ሰጥተዉ ያሳስራሉ። የፈለጉትን መሬት ለዉጭ አገር ዜጎች (ለእንደነ ሳዉዲዎች) በርካሽ ይሸጣሉ። የፈለጉትን እቃ ያለ ቀረጥ ያስገባሉ። የፈለጉትን ከአገር ያስወጣሉ ። ለዘመዶቻቸው ቢዝነስ ስለተፈለገ፣ ዜጎችን በግፍ አፈናቅለው ፣ የዜጎችን ቤት አፍርሰው በቦታዉ የነርሱን ሕንጻ ያሰራሉ። የፈለገ ወንጀል ሲሰሩ አይጠየቁም። እነርሱ በዊስኩ እጃቸዉን እየታጠቡ፣ ሌላዉ ወገናችን ግን ለስደት፣ ለጠኔ የተጋለጠ ሆኗል።

ምንም እንኳን ከኢሕአዴግ ዘንድ ሊታዩ የሚችሉ ጥቂት መልካም አዝማሚያዎች ላይ በር መዝጋት ባያስፈልግም፣ ምንም እንኳን ኢሕአዴግ ዉስጥ ያሉ ጥሩ ኃይላትን ማበረታቱ ጠቃሚ ቢሆንም፣ እንቁላሎቻችንን በኢሕአዴግ ቅርጫት ዉስጥ ብቻ ማድረጉ ግን ጉዳት አለው። የአገዛዙንም ርካሽ ፕሮፖጋንዳም ሆነ የድርድር ወሬ ከቁም ነገር መዉሰድ ያለብንም አይመስለኝም። ኢትዮጵያዉያን አንድ ዜና በመጣ ቁጥር፣ ወደዚህና ወዲዚያ እየነፈስን፣ ከዋናዉ ነገር ላይ ትኩረታችንን ማንሳት ማቆም ይኖርብናል። ዉጤት ከማያመጣና በስሜት ላይ ብቻ ከተመረኮዘ እንቅስቃሴዎች አልፈን መሄድ ይጠበቅብናል። በተለይም ደግሞ፣ አጠንክሬ የማሰምረበት፣ ሻእቢያ ወይንም ሻእቢያ ጋር ያሉ ቡድኖች ነጻ እንዲያወጡን አንጠብቅ። አሜሪካና አዉሮፓውያንም ጥቅማቸውን እንጂ ለኢትዮጵያ አያስቡም። «እናንተ ለመብታችሁ ካልታገላችሁ እኛ ምን አገባን ነዉ ?» ነዉ የሚሉት።

እግዚአብሄር በጸጋዉ የቸረንን፣ ጥቂቶች የሰረቁንን መብታችንን፣ ነጻነታችንና እኩልነታችንን የምናስጠብቀዉ እኛዉ እራሳችን ነን። በአሥር ሚሊዮኖች እንቆጣራለን። እያንዳንዳች ከልባችን «በቃ» ብንል፣ ለመብታችን ብንነሳ፣ ብንቆርጥ፣ ብንጨክን፣ የለበስነዉን ፍርሃት አዉልቀን ብንጥል፣ ለውጥ የማናመጣበት ምንም ምክንያት የለም። እኛን ማስፈራራትና መከፋፈል በመቻሉ እንጂ፣ ኢሕአዴግ እፍ ቢባል በቀላሉ የሚበን፣ የሞተና የበሰበስ ድርጅት ነዉ። እራሳችንን አሳንሰን አንመልከት። በዘር በሃይማኖት አንከፋፈል። ከአዲግራት፣ እስከ ሞያሌ፣ ከወልወል እሰከ አሶሳ፣ በቆላዉና በደጋዉ የአገራችን መሬት የምንኖር፣ በስደት በአለም ዙሪያ የተበተንን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ እንነሳ። ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ጥይት ሳይተኮስ፣ በሰለጠነ የፍቅር ፖለቲካ የኢትዮጵያን ትንሳኤ ማወጅ እንችላለን። ሰላማዊ በሆነ የእምቢተኝነት ዘመቻ የአገዛዙን ቀንበር መስበር እንችላለን። እየገደልን ሳይሆን እየሞትን አናሸንፋለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  “በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” ጥናት ትርጉም (117 ገጾች - ጥብቅ ምስጢር)

7 Comments

  1. girma kassa you are a confused MORON who dont know nothing but attacking g7 by anymeans as you are stupid arrogant and nonsense dude who dont know anything except screaming and crying agianst g7, in fact nonsense individuals like you and stupid qale paltalk rooms are the worest enemeies of not only udj and blue party but also to ethiopians in general, and who says supporting udj and blue party means attacking g7? moron….regardless of your senseless echo we ethiopians support every struggle against weyane and we support udj, blue party and g7 and others….down with the enemies of our struggle….

  2. @abel

    Come down we can see your shabia blood bawling too much. he just saying you can’t make change using remot control from 8000 miles or using Eritrian generals who are branded by UN human trafficking selling eritrian young body for a dollar to bring you freedom.

    • @ ethiopia

      first of all change your name to weyane or add confused as a title to describe your name…of course wheather you like it or not for we ethiopians the worst enemies are the weyane arrogant racist members and thier hodam servants as well as those stupid arrogant enemeies of our struggle like girma kassa and his qale paltalk room worst partners…

  3. Negotiation for reconciliation is not bad idea if the rulings party really did that. Ethiopia demands visionary, perceptive, and peaceful opposition, or collaboration if possible. However, in reality, what is being observed is duplication of parties with replicated idea, which is the result of contradictions within the parent parties. The country requires a party that could bring a change, harmony, development, and integrity to the nation. It is obvious that rule of single party can hardly bring fundamental change that the country requires; active involvement of all political stakeholders is basic requirement for national progression. However, fact-check shows that majority of opposition parties in Ethiopia and outside the country are lacking bandwidth that consists strategic ideology which the country strongly requires. It is not worthy to write about each individual party; however, as observant, it is essential to say few words about Ginbot-7
    As majority of Ethiopians know, the strategy of Ginbot-7 is the worst ideology for the country which is struggling with poverty. As the result of its worst outlook, the party has been neglected by many Ethiopians who really care about their country. Currently the party is attempting to regain the support from innocent citizens and other opposition parties via fabricated propagandas. The leader of Ginbot-7 was recently heard saying: releasing prisoners (in Ethiopia), involving other opposition parties, changing some governmental rules … are pre-condition to negotiate with the ruling party. At first place, where is the source for request for negotiation? Important thing that G-7 should know is the country has lots of keen people that would counter-check the hypothesis. This kind of thought is generated by underestimating the cognition level of entire nation.
    Some other instances:
    – Operation-Millennium: (a drama acted by some people and articulated by ESAT “journalists”), releasing such a fallacy drama to Ethiopians really indicates how their view to the people is deflated. They did not realize that majority of audiences are civilized enough to analyze not only the drama but also the intent behind. In their very drama, they mentioned that the communicators where located in different countries. Which telecom switch, base-station, or cellular link did they use to record the conversation that they have been acting? Even, do not need to challenge them technically; but, at least they should have looked for somebody who can well impersonate the government officials they were attempting to pretend in the drama. Their underestimation level to Ethiopian people is to the extent that Ethiopians cannot recognize even voices.
    – In G-7 party members meeting in USA: the party leader, Dr. Berhanu Nega, mentioned that he has no strategic plan so far for the country’s future, but he said his only intent is overthrowing the ruling party in Ethiopia. This is not right ideology that the country demands at this time. The nation is starving peace, integrity, and development; waiting for someone to design a plan after taking over the throne will not satisfy the requirements.
    – In the same meeting, another leadership member of the party, Mr. Andargachew Tsige, mentioned that he appreciates the opposition parties in home-country, which are peacefully struggling. He also added that the parties are paying big sacrifice (striking, jailing …..). That could be right. But it is very surprising that why Andargachew wouldn’t like to do what he admired (as long as possible). He admires peaceful opposition, but attempts to implement combat. Nobody can think that the sacrifice that opposition parties are paying in home country is as dangerous as battlefield combat that Andergachew is proposing to implement. Here is the thing: G-7 leaders have not been willing to pay as little sacrifice as the home-grown parties are paying by themselves. But they are planning to put others in a battlefield to combat and to move into the palace via blood-shading of innocents. Someone who is not willing to pay insignificant cost for freedom, but planning to go into palace through Bolle airport after incents shade blood, is not the one Ethiopia requires currently. Please do not attempt to propagate your propaganda by underestimating the cognition level of Ethiopians.

  4. I just wonder how much you receive for your trash comment like this one. you don’t have any moral to comment as such on those brave sons and doughters of Ethiopia. you might wonder how they will realize the birth of our beloved country we always call ETHIOPIA. please move aside and let them walk a walk of freedom and liberty.
    Time wont be to long for us to sing a song of freedom. please join us on this march. for now let me say this: how can you feel free by selling your humanity and moral for a money that even cant make your bosses strong.
    Join our march, a march that will even free you.

  5. @Ethiopia & Asrat
    Don’t forget to write about yours’ woyane’s drama( ETV dramas) & woyane’s human trafficing( trafficing of tens of thousends of poor womens & young girls per month to their barbaric areb lords.) Remember! Most of agencies are owened by woyane war lords and Tigrians. YOU GET IT ? Idiot zombies .

  6. Patriotism never expressed by grumbling; that is just a noise. However, if anyone could evidentially disprove the observations stated above, it would have been substantial. Don’t let your distraught to drive you blindly; rather use your mind to think rationally.

Comments are closed.

Share