March 30, 2018
4 mins read

በኦሮሚያ ከተሞች ትምህርት መቋረጡ ታወቀ

በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ውስጥ መደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት መቋረጡን መረጃዎች ጠቆሙ፡፡ በክልሉ ያለው የፖለቲካ አለመረጋጋት አሁንም በቀጠለባቸው ከተሞች ተማሪዎች የትምህርት ገበታቸው ላይ እየተገኙ አይደለም ሲሉ ያመላከቱ መረጃዎች፤ ችግሩን ወደ ቀድሞ ሁኔታው ለመመለስ የተደረገው ጥረት አለመሳካቱንም መረጃዎቹ ያክላሉ፡፡ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ዩኒቨርሲቲ መደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት መስተጓጎሉ የታወቀ ሲሆን፤ በተለይ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሙሉ በመሉ ተቋርጧል የሚያስብል ሁኔታ እንደተፈጠረ ተነግሯል፡፡ በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ከተቋረጠ ትንሽ ቆየት ማለቱን እና ተማሪዎቹን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ በመንግስት አመራሮች እየተደረገ ያለው ውትወታ ሊሳካ አልቻለም ይላሉ ከግቢው የወጡ መረጃዎች፡፡

የዩኒቨርሲቲው አስተዳደርም ሆነ ሌሎች የክልሉ መንግስት አመራሮች ተማሪዎችን በመሰብሰብ የተስተጓጎለው ትምህርት እንዲጀመር ያደረጉት የማግባባት ስራ ከሽፏል ሲሉም ይጠቁማሉ-መረጃዎቹ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአዳማ ከተማ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ከፍተኛ ደረጃ የሚማሩ ተማሪዎች ትምህርት ማቋረጣቸውን የጀርመን ድምጽ ዘግቧል፡፡ ዶይቸ ቬለ የአዳማ ከተማ ነዋሪን አነጋግሮ እንዳሰናዳው ዘገባ ከሆነ፣ በከተማዋ ከአንደኛ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ያሉ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ወደትምህርት ገበታቸው አልተመሰሉም፡፡ ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ጥያቄ ቢቀርብላቸውም ትምህርት ለመጀመር ፍላጎት እንደሌላቸው የገለጸው ዘገባው፤ ተማሪዎቹ ያቋረጡትን ትምህርት እንዳይጀምሩ የሚመክር በራሪ ወረቀት በአዳማ ከተማ እየተበተነ እንደሚገኝም ዘገባው ያስረዳል፡፡

ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ ሲካሄዱ በነበሩ ህዝባዊ ተቃውሞዎች ወቅት፣ ህዝብ ያነሳቸው ጥያቄዎች ካልተመለሱ በቀር ትግሉ እንደሚቀጥል እና የትግሉ አንድ አካል የሆነው ትምህርት የማቆም አድማም ጸንቶ እንደሚቀጥል ሲገለጽ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ራሱን ኮማንድ ፖስት እያለ የሚጠራው ቡድን በኦሮሚያ ክልል ግድያን ጨምሮ የእስር ዘመቻ በከፈተበት በዚህ ወቅት፤ የዩኒቨርሲቲ፣ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንደማይመለሱ በመግለጽ ላይ ይገኛሉ ሲሉ የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ መረጃዎቹ ሀሮማያን እና አዳማን በስም በመጥቀስ ትምህርት እንደተስተጓጎለባቸው ይግለጹ እንጂ፤ በሌሎች የክልሉ ከተሞችም መደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት መስተጓጎሉን የሚገልጹ ጥቆማዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡

BBN News March 30, 2018

Previous Story

ፈረስ ተቀይሯል!! ጋላቢው ማን ይሆን? – ጌድዮን በቀለ

women workers
Next Story

ምርኮኛ – አገሬ አዲስ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop