December 11, 2017
3 mins read

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ


(BBN) የጎንደር ዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ተቃውሞ አሰሙ፡፡ ተማሪዎቹ በዛሬው ዕለት ተቃውሞ እያሰሙ ከግቢው ለመውጣት ሲሞክሩ፣ ግቢውን በከበቡት ታጣቂ ፖሊሶች እና ወታደሮች ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተቃውሞ መነሻ፣ የትግራይ ተወላጅ በሆኑ የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተፈጸመው ጥቃት ነው፡፡ የዩኒቨርሲቲው ተማሪ የሆኑ የትግራይ ተወላጅ ተማሪዎች፣ በአማራ እና ኦሮሞ ተወላጆች ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ያስቆጣቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ ድርጊቱን በመኮነን ተቃውሞ ማሰማታቸውን እማኞች ገልጸዋል፡፡

ተቃዉሞን ተከተሎ የክልሉ ልዩ ኃይል ወደ ዩኒቨርሲቲው የሚወስዱ አውራ መንገዶችን በመዘጋጋት፣ አስለቃሽ ጭስ ሲተኩስ እንደነበር የገለጹት የዓይን እማኞች፣ ፖሊስ በወሰደው የኃይል እምርጃም ተማሪዎች መጎዳታቸውን እማኞቹ አክለው ተናግረዋል፡፡ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ በወንድሞቻችን ላይ የተከፈተው ጥቃት ይቁም በማለት ትምህርታቸውን ትተው ለተቃውሞ የወጡት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች፣ ጥያቄያቸው መልስ እስኪያገኝ ድረስ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንደማይመለሱም አስታውቀዋል፡፡

ከአዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ በአክሱም ዩኒቨርሲቲም ተመሳሳይ እና ዘር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየተፈጸመ እንደሚገኝ የገለጹት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ ጥቃቱ ያነጣጠረውም የአክሱም ዩኒቨርሰቲ ተማሪ በሆኑ የኦሮሞ እና አማራ ተወላጆች ላይ መሆኑን በመግለጽ፣ ድርጊቱን አውግዘዋል፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተነሳውን የተማሪዎች ተቃውሞ ተከትሎም፣ ዩኒቨርሲቲው ትምህርት መስጠት ማቆሙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ እስከ ምሽቱ ድረስም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በፖሊሶች ከበባ እንደተፈጸመበት ይገኛል፡፡

1 Comment

Comments are closed.

41373627 302
Previous Story

በኢትዮጵያ የተረጂዎች ቁጥር በመጨመሩ ተጨማሪ ስንዴ ሊገዛ ነው

Next Story

የለዉጥ ንቅናቄዎች በዛሬይቱ ኢትዮጵያ፦ ከየት፣ ወዴትና እንዴት? ሃሳብ ወለድ የኢትዮጵያዊያን ዉይይቶች

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop