የቅዱስ ዑራኤል ንግሥ ለ10ኛ ጊዜ በሚኒሶታ ተከበረ

July 29, 2013

(ዘ-ሐበሻ) ከተመሰረተ አስረኛ ዓመቱን ያከበረው የሚኒሶታው ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ ዛሬ የቅዱስ ዑራኤልን ዓመታዊ በዓል በደመቀ ሁኔታ አከበረ። በዚህ ለ10ኛ ጊዜ በተከበረው በዓል ላይ ብጹዕ አቡነ ሳሙኤል የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ የሚኒሶታ፣ የሳውዝ ዳኮትና የኮሎራዶ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስና፣ ሐዲስ ሐዋርያ አባ ወ/ትንሣኤ አያልነህን ጨምሮ በርከት ያሉ ካህናትና ዲያቆናት እንዲሁም በሚኒሶታና አካባቢው የሚኖሩ ምዕመናን እና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተገኝተዋል። በተለይም በዛሬው ዓመታዊ ንግሥ በዓል ላይ በዋልድባ ገዳም እየደረሰ ያለው የአባቶች ስቃይ የተነሳ ሲሆን በዚህም ላይ ከፍተኛ የሆነ የአባቶች ምስክርነት ተሰምቷል። ለምዕመናኑም ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በ4ኛው ፓትርያርክ አቡነ መርቆሪዮስ የሚመራውና በሚኒሶታ የዑራኤልና ኪዳነ ምህረትን ደብሎ የያዘው ይኸው ቤተክርስቲያን ለ10ኛ ጊዜ ዑራኤልን ባነገሰበት በዓል ላይ የተገኙት አባቶች ስለሰላም፣ ስለቤተክርስቲያን አንድነትና በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ በየገዳማቱ በአባቶች ላይ እየደረሰ ያለውንና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ላይ ስውር እጆች እያደረሱ ያሉት ጥፋቶች ሁሉ ለምዕመናኑ ተገልጿል።
የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ገብረሚካኤል ተሰማ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት ነሐሴ 1 (ኦገስት 7) ቀን የሚገባውን የፍስለታ ጾም በማስመልከት በየቀኑ በቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ ቅዳሴ እንደሚኖር ገልጸው ም ዕመናኑ በቅዳሴው ላይ እንዲገኝ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለፍልሰታ ጾም ፍቺም የኪዳነ ምህረት ዓመታዊ ክብረ በዓል በዚሁ ቤተክርስቲያን እንደሚደረግ አስተዳዳሪው ጨምረው ገልጸዋል።
የዛሬውን በዓል በከፊል የሚያሳይ ቪድዮ ደርሶናል – ተመልከቱት።

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop