Sport: ኢትዮጵያ ለቻን ዋንጫ አለፈች

July 27, 2013

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ደ ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2014 ዓ.ም ለምታስተናግደው የአፍሪካ ሀገሮች ሻምፒዮና (CHAN) ውድድር ለማለፍ የሩዋንዳ አቻውን ኪጋሊላይ በመለያ ምት 6 ለ 5 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በመጀመሪያው ጨዋታ አዲስ አበባ ስታዲየምላይ በአስራት መገርሳ ብቸኛ ጎል የሩዋንዳ አቻውን 1 ለ 0 ያሸነፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋሊያዎቹ የተሻለ እድል ይዘው ነበር ወደ ኪጋሊ የተጓዙት።

በጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ የጨዋታ እንቅስቃሴ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የነበረ ቢሆንም ተጨማሪ ጎል ማስቆጠር ሳይችሉ 0 ለ 0 የመጀመሪያ አጋማሽ ተጠናቋል። በሁለተኛ አጋማሽ ተመጣጣኝ የሆነ ፉክክር ያደረጉ ሲሆን በ68ኛው ደቂቃ ዋሊያዎቹን ሩዋንዳዎች ጎል አስቆጥረው ጨዋታው በአጠቃላይ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት 90ው ደቂቃ ተጠናቋል። ሁለቱን ሀገሮች ለመለየት በተደረገው የመለያ ምት ዋሊያዎቹ 6ለ5 በሆነ ውጤት የደቡብ አፍሪካ ትኬታቸውን ቆርጠዋል።

በፍጹም ቅጣት ምቱ የግብ ጠባቂው ሲሳይ ባንጫ ድንቅ ብቃት የታየበት ነበር። በጨዋታው ላይ ጉዳት የደረሰበት ጀማል ጣሰውን የተካው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሲሳይ ባንጫ ሁለት መለያ ምቶችን በማክሸፉም ከፍተኛ አድናቆትን እየተቸረው ይገኛል።

ጎሎቹን ለማየት ይኸው – ከኢትዮ ቲዩብ፦

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop