Sport: ኃይሌ ገ/ሥላሴ በ2007 ለወርቅ ሜዳሊያ ሣይሆን ለፓርላማ መቀመጫ ይሮጣል

July 23, 2013

(በአዲስ አበባ የሚታተመው ወርልድ ስፖርት ጋዜጣ እንደጻፈው)

ባለፉት 25 እና 26 አመታት በአለም የአትሌቲክ መድረክ ታላላቅ ውጤቶችን በማስመዝገብ አለምን ያስደመመውና ለወጣት አትሌቶች ተምሳሌት መሆን የቻለው ኃይሌ ገ/ስላሴ ፊቱን ወደ ፖለቲካው አለም ሊያዞር ነው፡፡ ኢትዮጵያን በፕሬዝዳንትነት መምራት እንደሚፈልግና የፓርላማ አባል ለመሆን እቅድ እንዳለው ዘ ኦብዘርቨር ከተባለው የእንግሊዝ ጋዜጣ ጋር ባደረገው ሰፊ ቃለ ምልልስ ገለፀ፡፡ የ40 አመቱ ጐልማሣ ኃይሌ ገ/ስላሴ በስፖርቱና በቢዝነሱ ተሣክቶለታል በቅርቡም ከፍተኛ የቡና እርሻ ጀምሯል፡፡ ከሁለቱ አመት በኋላ ደግሞ ፊቱን ወደ ፖለቲካው አለም በማዞር በ2007ቱ ሀገራዊ ምርጫ የግል ተወዳዳሪ ሆኖ እንደሚቀርብ ከጋዜጣው ጋር ባደረገው የስልክ ቃለ ምልልስ ጠቁሟል፡፡ ፕሬዝዳንት ለመሆን ትፈልጋለህ ወይ ተብሎ ጥያቄ የቀረበለት ኃይሌ ገ/ስላሴ ያንን ማን የማይፈልግ አለ ሲል ሀገሩን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ቁርጠኛ አቋም እንዳለው ተናግሯል፡፡ 547 መቀመጫ ያለውን የኢትዮጵያ ፓርላማ ለመቀላቀል በግሉ የሚወዳደረው ኃይሌ ገ/ስላሴ እድሉን ሊያገኝ እንደሚችልም ተንታኞች ከወዲሁ ይጠቁማሉ፡፡ በአሁን ወቅት በፓርላማው አንድ ግለሰብ በግል አባል ለመሆን መቻላቸው አይዘነጋም፡፡ እኚህ ግለሰብ የቀድሞ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕ/ት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ናቸው፡፡ ኃይሌ በ2007ቱ ምርጫ ፓርላማ የሚገባ ከሆነ ሁለተኛው የስፖርት ሰው ይሆናል ማለት ነው፡፡

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop