አንድነት ፓርቲ በፀረ -ሽብር ሕጉ ላይ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሊጀምር ነው

June 19, 2013

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከአራት ዓመት በፊት የፀደቀውን የፀረ-ሽብር ሕጉን ለማሰረዝና ይሄንኑ ሕግ ተላልፈዋል ተብለው በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲውን አመራሮችንና ጋዜጠኞችን ለማስፈታት በአይነቱና በይዘቱ ለየት ያለ ሕዝባዊ ንቅናቄ እንደሚጀምር አስታወቀ።
የፓርቲው የስራ አስፈፃሚ አባልና የሕዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ተፈራ በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት የአንድነት ፓርቲ የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ ሰለባ ከሆኑ ፓርቲዎች አንዱና ግንባር ቀደሙ መሆኑን በመጥቀስ አዋጁን ለማሰረዝ በሚሊዮን የሚቆጠር የሕዝብ የድጋፍ ፊርማ በማሰባሰብ አዋጁ ሕገ-መንግስቱን በግልፅ የሚጥስ መሆኑን ማስረጃ በማቅረብ ጭምር ክስ ለመመስረት መታቀዱን ተናግረዋል።
የህዝባዊ ንቅናቄ አተገባበሩን በተመለከተም በነገው ዕለት በፓርቲው ጽ/ቤት የፖለቲካ እስረኞች ቤተሰቦች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ወኪሎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ጋዜጠኞች በተገኙበት ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ንቅናቄው መጀመሩ በይፋ እንደሚበሰር አመልክተዋል።
ሕዝባዊ ንቅናቄው “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የሚጀመር ሲሆን ለቀጣዮች ሶስት ወራትም በተከታታይነት እንደሚቀጥል ከአቶ ዳንኤል ገለፃ መረዳት ተችሏል።
ፓርቲው ባስቀመጠው የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ መሰረት በአዲስ አበባና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች መዋቅሮቹን ሲያደራጅ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ ዳንኤል ሕዝባዊ ንቅናቄውን ትርጉም ባለው ደረጃ ማንቀሳቀስ የሚያስችል በአዲስ አበባ በ23ቱም ወረዳዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ ውጪ በዋና ዋና ከተሞች መዋቅር መመስረቱንም አረጋግጠዋል። የሕዝባዊ ንቅናቄውን ዓላማ ከዳር ሊያደርስ የሚችል ግብረኃይል መደራጀቱን አያይዘው አመልክተዋል።
ሕዝባዊ ንቅናቄው የሚካሄደው የድጋፍ ፊርማ በማዘጋጀት፣ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍና የአደባባይ ላይ ሕዝባዊ ስብሰባዎች በማካሄድ እንደሆነም አቶ ዳንኤል ገልፀዋል።

፦ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop