በባህርዳር ከተማ በብሄራዊ ቡድናችን ድል ደስታቸውን ለመግለጽ አደባባይ ከወጡት መካከል በአንድ መኪና ላይ ደስታቸውን ሆነው ሲገልጹ ከነበሩ ወገኖቻችን መካከል 2ቱ ሕይወታቸው ሊያልፍ መቻሉ ተዘገበ። በሌላ በኩልም – ኢትዮጵያ ትናንት ደቡብ አፍሪካን ማሸነፉዋን ተከትሎ ምሽት ላይ በነቂስ ወደ አደባባይ ወጥተው ድጋፍ ካደረጉት የባህር ዳር ነዋሪዎች መካከል በዛ ያለ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች “የኮከብ ዓርማ የሌለውን ሰንደቅ ዓላማ በመልበሳቸው፣ እንዲሁም ‹‹ሰማያዊ ፤ሰማያዊ ደገመው ዋልያዊ››፣ “ኢትዮጵያዊው ለሰንደቅ አላማው ፤ለሰማያዊው ” እያሉ ደስታቸውን በመግለጻቸው፣ ከፌደራል ፖሊሶች ጋር ውዝግብ ውስጥ ገብተው ማምሸታቸውን የኢሳት ቲቪ በዛሬ ምሽት የዜና እወጃው ዘገቧል።
ፖሊሶች ሰንደቅ ዓላማውን ለመንጠቅ ባደረጉት ሙከራ አንዳንድ ወጣቶችን መደብደባቸውን የዘገበው ኢሳት ወጣቶችም “ለባንዴራችን እንሞታለን” እያሉ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ አራት ወጣቶች ክፉኛ መደብደባቸውን የገለጸው የባህርዳሩ ወኪላችን፣ ‹‹ ፌደራል የፓርቲ ቅጥረኛ ገዳይ ነው፤ ፤የወንድሞቻችን ደም ፈሶ አይቀርም” በማለት አስፓልት ላይ ቆመው ሲናገሩ ተደምጠዋል ሲል ዘጋቢዎቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
በግርግሩ መሀል አንድ ሚኒባስ በመገልበጡ ሁለት ወጣቶች ሲሞቱ 4 ደግሞ መቁሰላቸውን የገለጸው ቲቪው የባህርዳር ከተማ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት ኢንስፔክተር ኢሳ ሁለት ወጣቶች መሞታቸውን ቢያምኑም ከሰንደቃላማ ጋር በተያያዘ ከፖሊስ ጋር ተፈጠረ የተባለውን ግጭት ግን አስተባብለዋል ብሏል።
በቡድናችን ድል ደስታቸውን ለመግለጽ አደባባይ ከወጡት መካከል መኪና ተገልብጦ ሁለት ሰዎች ሞቱ
Latest from Blog
ፋኖ ዝናቡ ልንገረው ለአገው ፈረሰኞች በዓል መልክት አስተላለፈ!
ፋኖ ዝናቡ ልንገረው ለአገው ፈረሰኞች በዓል መልክት አስተላለፈ!
ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ
“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::
እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!
በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት
ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!
ፋኖ አገዛዙ ላይ ከባድ ጥቃት ፈፀመ /የመቀለ ውጥረትና ታጣቂዎች የፈፀሙት /በኦሮሚያ ተደራጅታችሁ ታጠቁ ተባለ