በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምርጫ እንዲሳተፉ ሊደረግ ነው

June 12, 2013

በዘሪሁን ሙሉጌታ
በተለያዩ የውጪ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ዜጎች በሀገሪቱ በሚካሄዱ የምርጫ ስርዓት በመሳተፍ ድምፅ እንዲሰጡ ሊደረግ ነው።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ህግና ደንብ መሰረት በአረብ አገራት ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በአውሮፓ እንዲሁም ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ በሌሎች አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምርጫ መምረጥ የሚችሉበት ዕድል እየተመቻቸ ነው።
በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ተሳትፎ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ተሊል ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ምርጫው የሚከናወነው የሀገሪቱን አቅም ባገናዘበ ሁኔታ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው ማዕከላት ውስጥ የምርጫ ጣቢያዎችን በማደራጀት ዜጎቹ ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን እንዲወጡ ይደረጋል ብለዋል።
አዲስ የተዘጋጀው የዲያስፖራ ፖሊሲ ካካተታቸው ዋና ዋና ጉዳዮች አንዱ በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምርጫ እንዲሳተፉ ማድረግ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ቅዳሜ ሰኔ 8 ቀን 2005 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የዲያስፖራ ፖሊሲ ላይ በውጪ ሀገር ከሚኖሩ፣ ቁጥራቸው ከአንድ ሺ እስከ ሁለት ሺ ከሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ጋር በፖሊሲው ላይ ምክክር እንደሚካሄድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁ አይዘነጋም።n

 

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ጁን 12 ቀን 2013 ዕትም

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop