June 6, 2013
3 mins read

የአንድነት የወረዳ 19 ምክትል ሰብሳቢ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የወረዳ 19 ምክትል ሰብሳቢ ወጣት ባህሩ ራህመቶ ግንቦት 20/2005 ማለዳ ከመኖሪያ ቤቱ በደህንነት አባላት ከተወሰደ በኋላ የሚገኝበት ፖሊስ ጣብያ ሳይታወቅ ለቀናት መቆየቱንና በማረፊያ ቤቱ እንዲቆይ ያደረገው ፖሊስም እስከ ግንቦት 27/2005 ፍርድ ቤት ሳያቀርበው መቆየቱን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡
ሜክሲኮ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በ27/2005 እንዲቀርብ የተደረገው ባህሩ ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 17/2005 ሊያደርገው የነበረን ሰላማዊ ሰልፍ ስትቀሰቅስ ነበር የሚል ክስ እንደቀረበበት ለመረዳት ተችሏል፡፡የፍርድ ሂደቱን የባህሩ ወዳጆች፣ጋዜጠኞችና ታዛቢዎች በሚገኙበት ግልጽ ችሎት እንዲከናወን አለመደረጉም ብዙዎችን አስገርሟል፡፡ባህሩ ፍርድ ቤት በቀረበበት ዕለት የባለ ራዕይ ወጣቶች ማህበር ተቀዳሚ ፕሬዘዳንትና የህዝብ ግኑኝነት ሃላፊ የሆነው ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ለህዝብ ዝግ በሆነ ችሎት ጉዳዩን እንዲከታተል ተደርጓል፡፡
ፖሊስ የእነ ብርሃኑን ክስ ለመምራት የሚያስችለው ስልጣን እንደሌለው በመጥቀስ ሁለት ቀጠሮ የጠየቀበትን ጉዳይ ፍርድ ቤቱ እንዲዘጋለት ቢጠይቅም
ዳኛው የአዲስ አበባ ፖሊስ ክሱን ለፌደራል ፖሊስ እንዲያዞር በማዘዝ ክሱ ለፌደራል ፖሊስ ካልዞረ ግን በ29/5/2005 መዝገቡን በመዝጋት ተጠርጣሪዎቹን በነጻ እንደሚያሰናብቱ አስረድተዋል፡፡የእነ ብርሃኑ ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ‹‹ፍርድ ቤቱ ከፖሊስ የቀረበለትን ጥያቄ በመቀበል ያለ በቂ መረጃ እየተንገላቱ የሚገኙትን ደምበኞቻቸውን በነጻ ማሰናበት ሲገባው ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ እንዳስገረማቸው ገልጸዋል፡፡
የባህሩና የብርሃኑ ቤተሰቦችና የቅርብ ሰዎች ነገ በሚካሄደው የፍርድ ችሎት ሁለቱ ወጣቶች በነጻ ሊሰናበቱ እንደሚችሉ ተስፋ ማድረጋቸውን ለፍኖተ ነጻነት ተናግረዋል፡፡
source:- http://www.fnotenetsanet.com/?p=4543
Likun astatke jpg
Previous Story

ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ ተከሰሱ

UDJ Candlelight vigil
Next Story

ኑ! በገዢው ቡድን በግፍ የተጨፈጨፉ ሰማዕታትን በመዘከር የትግል ቃልኪዳናችንን እናድስ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop