በኖርዌይ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቸ ኮራሁ፤ ለኢትዮጵያ የጉብኝት ዘመን ደረሰ ይሆን?

ዳንኤል ከኖርዌይ
ይህንን ጽሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ april 28,2013 በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ የወያኔ ተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ያየሁትና የሰማሁት የኢትዮጵያውያን ጩኸት ነው። በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የወያኔ ግፍ ያንገፈገፋቸው ኢትዮጵያውያን ይጮሃሉ፥ኦሮሞው ይጮሃል፣ አማራው ይጮሃል፣ ጉራጌው ወዘተ ይጮሃል። ሴቱ ይጮሃል፣ወንዱ ይጮሃል ሙስሊሙ ይጮሃል፣ክርስቲያኑ ይጮሃል…. ኧረ የማይጮህ የለም ሁሉም ሰው ይጮሃል።

በኖርዌይ ያሉ ኢትዮጵያውያን ጩኸት ግን የእነርሱ ብቻ ጩኸት ሳይሆን በአለም ዙርያና በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትም ኢትዮጵያውያን ጩኸት ጭምር ነው። ከወያኔና ከደጋፊዎቻቸው ዉጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ጩኸት ነዉ።ግፍ በቃን፥ዘረኝነት በቃን፥አፓርታይድ በቃን፥ፉሺዝም በቃን የሚል ጩኸት፣ ከአንደበት ብቻ ሳይሆን ከልብ የሚወጣ ጩኸት።

ኢትዮጵያዊዉ በየበረሃው ይጮሃል፣በሲና በረሃ ሆዱ እየተቀደደ ሆድ ዕቃው እየወጣበት ይጮሃል፥ ወደስደት ሲነጉድ በየመንገዱ በአውሬ እየተበላ ይጮሃል፥የሚጓዝባት ጀልባ እየሰጠመች በሞት ጥላ መካከል ሆኖ ኢትዮጵያውያዊው ወገኔ ይጮሃል፣በተለያዩ ሃገራት እስር ቤቶች የታጎሩ ሴትና ወንድ ኢትዮጵያውያዊያን ይጮሃሉ።

በየአረብ አገራት ለዘመናዊ ባርነት ተሽጠው ከአሰሪዎቻቸው ግፍ የተነሳ በፈላ ዘይት እየተቃጠሉ ይጮሃሉ፣በአለንጋ እየተገረፉ ይጮሃሉ፣ ከፎቅ ላይ እየተወረወሩ ይጮሃሉ፣ የጉልበት ዋጋቸውን ተነጥቀው ይጮሃሉ፣ በወሮበሎች እየተደፈሩ ይጮሃሉ ሌሎቹም ህጋዊ ፈቃድ የላችሁም ተብለው እየተሳደዱ ይጮሃሉ፣

በኢትዮጵያ ውስጥ የዘር ማጥፉት ሰለባ የሆነው የአኙዋክ ወገኖቻችን ይጮሃሉ፣ አማራ ነህና በዚህ አትፈለግም ተብሎ በግፍ ከየስፍራው እየተሰደደ ያለው ወገኔ በየእስር ቤቱ የተጋዘው ኦሮሞ ወገኖቼ ይጮሃሉ፣ እውነትን በመጻፉቸውና በመናገራቸው ብቻ እስከሞት ድረስ የተፈረደባቸው ወገኖቼ ይጮሃሉ፣ በዋልድባ እየተገረፉና እየተሰደዱ ያሉ መነኮሳት ይጮሃሉ፣አብርሃና አቶ አስገደ ከትግራይ ይጮሃሉ ኧረ ዛሬማ የሚገርም ነገር ሰማሁ አባመላ የተባለ በዳያስፓራ ቀንደኛ የወያኔ ሰው ይጮሃል ሲባል።አሁንማ ማን የማይጮህ አለ? ሁሉንም የሚያስጮኸው ግን አንድ ነገር ነው፣የወያኔ ግፍ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ባንዲራው የ ‘ሁላችንም’ ነው!! – ታሪኩ አባዳማ

የኖርዌይ ኢትዮጵያዊያን ጬኸት የወያኔን ሹማምንትና ደጋፊዎች አዋርዶ እኛን ኢትዮጵያዊያንን አኩርቷል። እያሪኮን እንዳፈረሰው የእስራኤላዊያን ጩኸት ነበር።

ለእኔ ግን ለኢትዮጵያ የጉብኝት ዘመን ደረሰ ይሆን? የሚል ጥያቄ አስነሳብኝና የእስራኤላዊያን በግብፅ 400 ዓመት የባርነት ህይወት በኋላ የነፃነት ዘመን ሲደርስ የነበረው ሁኔታ ከአሁኑ የአገራችን ሁኔታ ጋር ተመሳስሎብኛልና ምስስሉን ከመፅሃፍ ቅዱስ እያጣቀስኩ ላሳይ፥

1. እግዚአብሄር ለአብርሃም የገባው የተስፉ ቃል-ዘርህ ለእርሱ ባልሆነች ምድር ስደተኞች እንዲሆኑ በእርግጥ እወቅ፤ ባሪያዎች አድርገውም አራት መቶ ዓመት ያስጨንቋቸዋል።
ደግሞም በባርነት በሚገዙአቸው ሕዝብ ላይ እኔ እፈርዳለሁ፤ ከዚያም በኋላ በብዙ ከብት ይወጣሉ።(ዘፍጥረት 15፥13)

እግዚአብሄር ለኢትዮጵያ የገባው የተስፉ ቃል-ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች። (መዝሙር 68፥31)

2. የእስራኤላዊያን መከራ በግብፃውያን ገዢዎቻቸው-ግብፃውያንም የእስራኤልን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ሥራ፥ በጭቃ፥ በጡብም በእርሻም ሥራ ሁሉ፥ በመከራም በሚያሠሩአቸው ሥራ ሁሉ፥ ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው ነበር።(ዘፀአት1፥13-14)

የኢትዮጵያዊያን መከራ በወያኔ ገዢዎቻቸው-ወያኔዎችም የኢትዮጵያን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ዘረኝነት፥ በስደት፥ ከስፍራ በማፈናቀል ሁሉ፥ በእስር ሁሉ፥ ሕይወታቸውን ያስመርሩአቸው ነበር።

3. የእስራኤላዊያን ጩኸትና በእግዚአብሔር መደመጥ -ከዚያም ከብዙ ቀን በኋላ እንዲህ ሆነ፤ የግብፅ ንጉሥ ሞተ፤ የእስራኤልም ልጆች ከባርነት የተነሣ አለቀሱ፥ ጮኹም፥ ስለ ባርነታቸውም ጩኸታቸው ወደ እግዚአብሔር ወጣ።(ዘፀዓት 2፥23)

የኢትዮጵያዊያን ጩኸትና በእግዚአብሔር መደመጥ-ከዚያም21 አመት በኋላ እንዲህ ሆነ፤ የወያኔ ንጉሥ መለስ ሞተ፤ የኢትዮጵያ ልጆች ከባርነት የተነሣ አለቀሱ፥ ጮኹም።

4. እግዚአብሔርም የለቅሶአቸውን(የእስራኤላዊያንን) ድምፅ ሰማ፥ እግዚአብሔርም ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን አሰበ።(ዘፀዓት 2፥24)

ታዲያ ወገኖቸ ይህ የኢትዮጵያዊያን ጩኸት በእግዚአብሄር ዘንድ ይሰማል የሚል እምነት አለኝ።ያን ጊዜ ደግሞ እንዲህ ይሆናል፣
እግዚአብሔርም የለቅሶአችንን ድምፅ ይሰማል፥ እግዚአብሔርም ከኢትዮጵያዊያን ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን ያስባል ።
የእስራኤላዊያንን ነፃነት የሰጠ እግዚአብሄር ለኢትዮጵያዊያንም ነፃነታችንን እንድንጎናፀፍ ይረዳናል። እኔ ለኢትዮጵያ የጉብኝት ዘመን እንደደረሰ አምናለሁ፥እስከዛው ጬኸታችንን እንቀጥል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ያለፉት ሃያ አንድ ዓመታት ፖለቲካ - ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

የኖርዌይ ኢትዮጵያዊያን በእናንተ ኮርቻለሁ፣በርቱ።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

2 Comments

  1. The real solution for our country problem is Lord and God Jesus Christ. As long as we do not exactly know the enemy Demon we will still crying. How long we blind can not see, we the deaf can not hear the work of almighty God? God is better than UN, the US, and all the militarly strog nations why not we march on the street by the name of Lord and God Jesus Christ and see the reasult with intersting and amusing. Why you blind and deaf unbelievers forget our God? You will still cry …….. remove your Idol; stop worshiping developed for nothing countries. take an easy step, just easy, get together speak to the most high God the God the holy of Israel. Why you forgot Demon? It is all about Demon how long we fight blood and flesh?
    God is great great all the time all this hell is because of our sin our Idol we know worshiping people than God so we will cry we will suffer all the time.

Comments are closed.

Share