October 7, 2024
4 mins read

የፋሽስቱ አብይ አህመድ አሊ ኢትዮጵያ ውስጥ በአማራ ላይ እየተካሄደ ስለሚገኘው ጦርነት ከመስከረም 13 እስከ 27/2017 ዓ.ም በተለያዩ ቦታዎች ላይ የደረሰ የጉዳት !!!መረጃ:

462285684 861253652803598 6644509506161987591 n
ሸዋ
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በደራ ወረዳ ልዩ ስሙ ኮሉ በተባለ አካባቢ ላይ በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ላይ አሸባሪው የሸኔ ቡድን ከኦሆዴዱ ጥምር ጦር ጋር ቅንጅት በመፈጠር መስከረም 22 ቀን 2017ዒ.ም ከለሊቱ 11:00 እስከ 12:00 ድረስ ከፍተኛ ጉደት አድርሷል።
አሸባሪው ሀይል ጨለማን ተገን በማድረግ በርካታ ንፁሀን ገድሏል፣ ቤቶችን አቃጥሏል፣ ንብረት ዘርፏል፣ በርካታ የቁም እንሰሳትን ሲወስድ ሰዎችን አግቶ ወስዷል።
ከ 500 በላይ የቁም የእንስሳት ከብቶችን ዘርፎ ወስዷል
ከ 6 በላይ ቤቶችን በእሳት አቃጥለዋል
7 ሰዎችን የገደሉ 3 ይታገቱና የወሰዱ ( 2 እናቶችን እና 1 ህፃን)
ጎጃም:
የአገዛዙ ጦር በጣለው ሞርታር አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል::
የአገዛዙ ጦር ዛሬ መስከረም 23 ንፁሀንን አላማ አድርጎ በጣለው ሞርታር የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ አራት ንፁሐን ላይ የአካል ጉዳት አድርሷል። ኮሶበር ሆኖ ወደ መኖሪያ መንደሮች በተጣለው ሞርተር ሳትማ ዳንጊያ በተባለ ስፍራ በንፁሀን ቤት ላይ በማረፉ የአንድ ቤተሠብ አባላት የሆኑ አራት ሰዎች ላይ ወላጅ እናትና ህፃን እንዲሁም እንስሳትን ጨምሮ የአካል ጉዳት ደርሷል።
ጉዳቱ የደረሰባቸው
1.መሠንበት ተስፋው 3. አቶ ተስፋው ጌታሁን(አባት)
2.ሙሉነህ ተስፋው 4. ወ/ሮ ቀኑ ፈቃዱ(እናት) የተባሉ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው።
በተመሳሳይ በአገዛዙ ሠራዊት በተፈፀመው ጥቃት አንድ ፈረስ እና 13 የቀንድ ከብቶች ተገለዋል።
የአገዛዙ ሠራዊት ከፋኖ የገጠመውን ደፈጣ መቋቋም ሲያቅተው የቡድን መሣሪያዎችን ወደ መኖሪያ መንደሮች እየተኮሰ ንፁሀንን እና የእንስሳ ከብቶችን እየገደለ ይገኛል::
ጅጋ ላይ ለ6ተኛ ጊዜ የሄሌኮፍተር ጥቃት ያደረሰ ሲሆን በሰውና በንብረት ላይም ጉዳት አድርሷል::
ሜጫ ወረዳ ዳጊ ጤና ጣቢያ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ እያለ የጤና ባለሙያዎች እና ታካሚ ህዝብን ጨፍጭፏል::
ወሎ
በደቡብ ወሎ ዞን ኩታበርና አንባሰል ድንበር ዚሃ በተባለ አካባቢ በሰብል ስብሰባ ላይ በነበሩ አርሶአደሮች በተተኮሰ ጥይት ስድስት (6) ንፁሀን አርሶአደሮችን ገድሏል::
ፋኖ በአካባቢው በሌለበት ቤትለቤት በመዞር ንፁሀንን እያንገላታና ወጣቶችን በማሰር ላይም ተጠምዷል::
ጎንደር
እብናት እና አካባቢው ከ4 ጊዜ በላይ የአየር ድብደባ ተካሂዷል:: በዚህም በርካታ ንፁሀን እየተጨፈጨፉ ነው::
ቋራ ወረዳ ሽንፋ ቀበሌ የድሮን ጥቃት በማድረስ 7 (ሰባት) ንፁሀንን ሲገድል ሰብሉንም አውድሟል::
በዚሁ በሽንፋ በቀን 23/01/2017 በገበያ ላይ በተጣለ የድሮን ጥቃት ከ16 ንፁሀን በላይ ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ ከ20 በላይ ቆስለዋል:: ቁጥሩ ያልታወቀ በርካታ ቤቶችም በዚሁ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል::
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ፣ አዊ፣ ደቡብ ጎንደር፣ጎጃም ፣ ማዕከላዊ ጎንደር እና ምዕራብ ጎንደር ዞኖችን ጨምሮ በትንሹ 7 የዞን አስተዳደሮች ላይ የሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት ጨምሮ ጭፍጨፋ አካሂዷል::

የዳላስ አማራ ማህበር

Leave a Reply

Your email address will not be published.

mebre mengiste yesew telalak
Previous Story

መብሬ መንግስቴ – የሰው ተላላኪ (Mebre Mengiste – Yesew Telalaki) – New Ethiopian music 2024(official video)

Killer Abiy Ahmed
Next Story

የጨካኝ ገዥዎች እና የአድርባዮች የቤተ መንግሥት ፖለቲካ

Latest from Blog

blank

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ
blank

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ
blank

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop