October 1, 2023
5 mins read

የጠለምት አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ መምህር ፀጋዬ እሸቴ በግፍ መታፈን አስመልክቶ ከልሳነ ግፉዓን ድርጅት የተሰጠ መግለጫ

Lisane Gufuan 2 1ፋሽስቱ ትህነግ/ወያኔ በኢትዮጵያ ጀግኖች ልጆች ብርቱ ክንድ ተደቁሶና እጁ ተጠምዞ ጥቅምት 23/2015 ዓ.ም ፕሪቶሪያ ላይ የሰላም ስምምነት እንደፈረመ ይታወቃል። ይህ ባለ 15 አንቀፅ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ አመት ሊሞላው ከወር ያነሰ እድሜ የቀረው ቢሆንም የስምምነቱ ክፍሎች በሙሉ ተጥሰውና ትህነግ/ወያኔ ዳግም የህዝባችን የህልውና ስጋት ወደ መሆን እንዲሸጋገር የተደረገበት የክህደት ቁልቁለት ላይ እንገኛለን።

በአሁኑ ወቅት በዘር ማጥፋትና በሀገር ክህደት ወንጀሎች የሚፈለጉት የትህነግ/ወያኔ መሪዎች በተለየ ጥበቃና እንክብካቤ አዲስ አበባ ላይ እየተንጎማለሉ፤ በአንፃሩ ደግሞ ንፁሃን የአማራ ምሁራን፣ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ ባለሃብቶችና፣ በተለይም ወጣቶች በጅምላ እስር እየተሰቃዩና መከራን እየተቀበሉ ይገኛል። የአማራ ልጆች በገፍና በግፍ መታሰርና መሰቃየት ዋነኛው ምክንያት የብልፅግና መንግስት በአማራ ህዝብ ላይ የፈፀመውን ታሪካዊ ክህደትና ከትህነግ/ወያኔ ጋር የገባበትን መርህ አልባ ግንኙነት ያደናቅፋሉ በሚል እንደሆነ ልሳነ ግፉዓን በፅኑ ያምናል።

የመምህር ፀጋዬ እሸቴ አፈና የብልፅግና መንግስት የገባበትን የአማራ ፖለቲከኞችንና መሪዎች የማሳደድና ብሎም የማጥፋት ዘመቻ አንዱ ማሳያ ነው። መምህር ፀጋዬ እሸቴ በግፍ እስከ ታፈኑበት እለት ማለትም መስከረም 3/2016 ዓ.ም. ድረስ የጠለምት አማራ ማንነትና የወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ። መምህር ፀጋዬ እሸቴ የታፈኑበት ምክንያት በውል ባይታወቀም በአዳርቃይ ከተማ መከላከያ ጦር ሰፈር የቴክኒክ ሞያ ውስጥ በግፍ ታስረው እንደሚገኙና ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ መረጃ ደርሶናል።

የመምህር ፀጋዬም ሆነ የሁሉም የአማራ ልጆች የጅምላ እስርና ስቃይ የሚመነጨው የብልፅግና መንግስት ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ራያና አካባቢውን ከፕሪቶሪያው ስምምነት ውጭ ለትህነግ/ወያኔ አሳልፎ ለመስጠት የሸረበውን ሴራ ያደናቅፋሉ በሚል እንደሆነ እናምናለን። ለዚህም ዋና ማሳያው እነ መምህር ፀጋዬን የመሰሉ የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጆች እንዲያፍኑና እንዲያሰቃዩ ተላልፈው የተሰጡት በቅርቡ ወደ ሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዲቀላቀሉ ለተደረጉ የትህነግ/ወያኔ ነባር ታጋዮች መሆኑ ነው።

ልሳነ ግፉዓን ድርጅት ደግሞ ደጋግሞ እንደሚያሳስበው የብልፅግና መንግስት በአማራ ህዝብ ላይ የጀመረውን የጅምላ እስርና ማሰቃየት በአስቸኳይ ካላቆመ ሀገር ወደ ከፋ ምስቅልቅልና ቀውስ ውስጥ ትገባለች የሚል ስጋት አለን::

ይህ ሀገራዊ ምስቅልቅል ሁሉንም የኢትዮጵያ ህዝብ በከፋ ሁኔታ የሚጎዳና የትኛውም የህብረተሰብ ክፍል ከመጣው ሀገራዊ አደጋ ተለይቶ እንደማይተረፍ ማስገንዘብ እንወዳለን።

ስለሆነም የብልፅግና መንግስት በግፍና በማን አለብኝነት ያፈናቸውን መምህር ፀጋዬ እሸቴንና ሁሉንም የአማራ ልጆች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈታና ለሀገራዊ መረጋጋትና ሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲሰራ እናሳስባለን።

 

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይባርክ!

በአማራ ህዝብ ላይ የተከፈተው የዘር ፍጅት በአስቸኳይ ይቁም!

Lisane Gufuan 1 1

ልሳነ ግፉዓን ድርጅት

መስከረም 29/2016 ዓ.ም.

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

186154
Previous Story

ዐቢይም እንደ ቦካሳ ሰዎችን እያሳረደ | አንድ ሻለቃ ጦር ተደመሰሰ | አሜሪካ ፋኖን የሰለለችበት የሳተላይት መረጃ

5688966979 1 1
Next Story

ከአማራ ፋኖ፣ ከኢትዮጵያ ፋኖ፣ ይድረስ ለሎንዶን ፋኖ!!! ሚሊዮን ዘአማኑኤል (ኢት-ኢኮኖሚ)

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop