July 11, 2022
3 mins read

2 የአዳነች አበቤ ካቢኔ አባላት በኮንደሚኒየም እጣ ማጭበርበር ተጠርጥረው ታሰሩ

3433333ሁለት የአዳነች አበቤ የካቢኔ አባላት፣ አቶ ሙሉቀን እና የቤቶች ልማት ቢሮ ወ/ሮ ያስሚን፣ ከኮንዶሚኒየም እጣ ጋር በተያያዘ ለማጭበርበር ሞክረዋል ተብለው ትላንት ማታ ታስረዋል።
እንደሚታወቀው፣ ይህ የባልደራስ የፌስቡክ ገፅ፣ እጣው ከወጣ ቦኃላ ውጤቱ እንዳይነገር ከተደረገበት ግዜ አንስቶ ቀዳሚውን ተቃውሞ ከማንሳቱም ባሻገር፣ ጥቆማ እየተቀበለ ሸፍጥ እየተሰራ መሆኑን ቀድሞ አጋልጧል። በዚህ እንቅስቃሴውም፣”ኦሮሞ ጠል ነው” ተብሎ ተተቸቷል።
ይህ ገፅ ቀደም ብሎ ባወጣው ዘገባ፣ “የኦሕዴድ ካድሬዎች በልዩ ሁኔታ ኮንዶሚኒየም እንዲሰጣቸው በተቀመጠው አሰራር ፈፅሞ እንዳልረኩ ታውቋል። በግልፅ ይደረጋል የተባለው የባለ እድለኞች እጣ አወጣጥ፣ ከመጋረጃ ጀርባ አሁንም በተረኞች ተጠልፎ ውዝግብ እና ቅሬታ እያስነሳ ይገኛል። ማሽኑ ያወጣው ዕጣ ለሕዝብ ይፋ ከመሆኑ በፊት በሰዎች ሳንሱር እየተደረገ ይገኛል” ብሎ ነበር።
በዚህ ሂደት ሁለት ሰዎች አሁን ለእስር የተዳረጉ ቢሆንም፣ በከንቲባዋ አቀናባሪነት የሚመራው ዋነኛው የኦህዴድ/ ብልፅግና የተረኞች ቡድን ገና ለህግ አልቀረበም። ከሸፍጡ በስተጀርባ ያለው ዋናው ይህ ቡድን ነው።
በዚህ ቡድን ቁጥጥር ስር ያለው የአዲስ አበባ አሰተዳደር ትላንት ምሽት ተገዶ ባወጣው መግለጫ፣ “ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው፣ የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል፡፡
በመሆኑም፣ በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ፣ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡ በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል፡” ብሏል።
ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁት ይህን ዜና ከሰሙ ቦኃላ በሰጡት አስተያየት፣ ከንቲባዋስ? ብለው ጠይቀዋል።
ቀጣይ ዘገባዎችን ይዘን እንመለሳለን።
ዘገባው—-ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ

1 Comment

  1. የወ/ሮ አዳነች አቤቤ የ50ሚሊዮን ዶላር ወድ አካውንታቸው የገባው በኦሮምያ ስብሰባ የተገመገሙበት ጉዳይ ከመን ደረሰ?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

welkeit
Previous Story

ለወልቃይት፤ ሐምሌ-05 ምስክር ትሁን! – በሙሉዓለም ገ/መድኀን

291933820 547696883702799 3404627951328916657 n 1
Next Story

አሸባሪ የኦነግ እና የትሕነግ ኃይሎች በኤፍራታ እና ግድም ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ላይ የተደራጀ የወረራ ጥቃት ከፍተዋል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop