November 12, 2020
2 mins read

ታሪክ ሥራ አለብህ (ዘ-ጌርሣም)

ታሪክ ሥራ አለብህ
መስካሪ ነህና ነገ ጧት በተራህ
ይዘጋጅ ብራናው
የገድል መክተቢያው
ሾል ይበል ብዕሩ
ይቀለም መስመሩ
መዝግብ የሆነውን
አገር ያወቀውን
ፀሐይ የሞቀውን
የሰበሰብከውን በገደል በዱሩ
የኢትዮጵያ ጀግኖች እንዴት እንዳደሩ
ታሪክ ሥራ አለብህ
የሰበሰብከውን መዝግበው እባክህ
በጥብጠው ቀለሙን
አሹለው እርሳሱን
መዝግበው ድርጊቱን
አዘጋጅ ጠልሰሙን
ክተበው እልቂቱን
አስቀምጥ ታሪኩን
የተሠራውን ግፍ
የወገንን መርገፍ
በጥይት መደብደብ
ያለምንም ገደብ
በጭካኔ መንፈስ
ሰውን በሚያረክስ
ያገር ሀብት መዘረፍ
የዘር ማፅዳት ግፉን
በየጉራንጉሩ አርበኛ መሞቱን
የሃገር ዋቢውን
መከላከያውን
እንዴት እንዳጠቁት
ያውም ከተኛበት
አንገት ያስደፋውን
ቅስም የሰበረውን
አረመኔ ድርጊት
በዚህ የቅስፈት ወቅት
በአገር ከሃዲዎች
ወጭት ሰባሪዎች
የተሠራውን ግፍ
ለትውልዱ ይትረፍ
ያኑረው በሃፍረት
በማስደፋት አንገት
ታሪክ ሥራ አለብህ
ያዝ ግፉን መዝግበህ
ዕውነት ቢድበሰበስ
በውሸት ቢቸለስ
ሐቅን እትፍ ካልህ
ተጠይቂ አንተ ነህ
ታሪክ ሥራ አለብህ
ስንክሣሩን ያዘው እጅግ ተጠንቅቀህ
የሚተካው ትውልድ ስለሚጠይቅህ
2020-11-11

Leave a Reply

Your email address will not be published.

112542
Previous Story

አፋኙ ህወሓት በመከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲያደርሱ የላካቸው የልዩ ሃይል አባላት እጃቸውን የሰጡበትን ምክንያት ለኢቲቪ አጋርተዋል

Next Story

   በደልን ይቅር የሚል፣- ጆቢር ሔይኢ ከሁስተን ቴክሳስ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop