ዶ/ር አብይን በእውቀት እንወቅ – ዶ/ር ዘላለም እሸቴ

የኢትዮጵያ ነገር መላ እንደሌለው፤
አምላኳ አወቀላት ጉዳዩ ሌላ ነው።

ብርሃን ፈነጠቀ ዶ/ር አብይ መጣ፥
ኢትዮጵያን ሊታደግ እርሱ እንቅልፍ አጣ፥
ሁሉም ደገፈና አንድ ላይ ሰልፍ ወጣ፥
ልናርፍ ነው ብሎ ከነበረን ጣጣ።

ቃሉ የሚጣፍጥ የሌለው ወደር፥
ትህትናው ግሩም ልዩ ከምድር፤
ፅናቱ የሚገርም ደግሞም እይታው፥
ድፍረቱ ትጋቱ እጅግ የሚደንቀው።

ጠላቱ እያደር እየበዛ ሲሄድ፥
ወደድኩህ ያለውም ሊያወጣው ከመንገድ፤
ከወዲህ ከወዲያ ሁሉም ሲጎትተው፥
ስምም እያወጣ ቢጎነታትለው፤
ዝም ብሎ ነጎደ አልተነቃነቀ፥
ሁሉንም እያየ አውቆም እያወቀ።

የኢትዮጵያ ነገር መላ እንደሌለው፥
አምላኳ አወቀላት ጉዳዩ ሌላ ነው፤
ጠላቶቿ በዙ እጅግ ጨከኑባት፥
ስለዚህ ወረደ አምላክ ሊፈርድላት፥
ምድር ዝም ትበል ይታይ ሲለይለት።

ትዕግስት አይጠቅመንም ቶሎ ያልቃልና፥
ተስፋም አይረዳንም ስጋት ያንቃልና፤
ይልቁንስ እንይ የማይታየውን፥
በእውቀት እንወቅ አይለፈን ይህ ቀን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ወያኔ ጠላቴ ነዉ ያለዉ አማራን እንጅ ኢትዮጵያን አይደለም::አንተ ከዬት አምጥተህ ነዉ ወያኔ የኢትዮጵያም ጠላት ነዉ እያልክ የምትጽፈዉ?  - ሸንቁጥ አየለ

1 Comment

  1. የዶ/ር ዘላለም እሸቴ ግጥም የድንቁርናውን ጠርዝ ፍንትው ኣድርጎ ያሳየናል !!!!

Comments are closed.

Share