መድረክ በሳዑዲ መንግስት ላይ ስልፍ እንዳይወጣ በከለከለው ኢሕአዴግ ላይ ሰልፍ ሊወጣ ነው

– ሰላማዊ ሰልፉ ለህዳር 29 ተጠርቷል

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ጉዳት በመቃወም በሳዑዲ አረቢያ መንግስት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ቢጠራም መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ይካሄዳል፤ በቂ የፖሊስ ኃይል የለኝም የሚል ምላሽ መስጠቱን ተከትሎ መድረክ ተቃውሞውን በኢትዮጵያ መንግስት ላይ እንደሚያደርግ ገለፀ።
የአራት ፓርቲዎች ግንባር የሆነው መድረክ የተቃውሞ ሰልፉን በተመለከተ በመንግስት የተሰጠው ምላሽ የማያሳምንና የሕዝብን ብሦት በተዘዋዋሪ መንገድ የሚያፍን ተግባር በመሆኑ የሳዑዲ አረቢያ መንግስትን ለመቃወም ከሚደረገው ጥረት ጎን ለጎን የተቃውሞ ሰልፉ ሕዝብን እያፈነ ባለው መንግስት ላይ ማነጣጠሩን የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል።

ሰልፉ በመጪው ህዳር 29 ቀን 2006 ዓ.ም መነሻውን ስድስት ኪሎ የመድረክ ጽ/ቤት አድርጎ መድረሻውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት እንደሚሆን ዶ/ር መረራ ጨምረው ገልፀዋል።
“የኢትዮጵያ መንግስት የሳዑዲ አረቢያን መንግስት እንዳንቃወም አድርጎናል።” ያሉት ዶ/ር መረራ የኢትዮጵያ መንግስት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሕዝቡን ብሦት በተቃውሞ እንዳይገልፅ አድርጓል። የኢትዮጵያ መንግስት ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር ባለው ፍቅር ይሁን በሌላ ምክንያት ለጊዜው ግልፅ ባልሆነልን ምክንያት ተቃውሞአችንን በመከልከሉ የአሁን ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት ላይ ያተኮረ ነው ሲሉ ዶ/ር መረራ ተናግረዋል።
እስከአሁን ባለው ሂደት መንግስት ሕገ-መንግስታዊና ሰብአዊ መብት የሆነውን ተቃውሞን በሰልፍ የመግለፅ መሠረታዊ መብት አሳማኝ ባልሆነ መንገድ በመጣስ እየተረባረበ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር መረራ ሕዝቡም ይህንኑ እንዲገነዘብልን ሲሉ ጠይቀዋል። “በአውሮፓና በአሜሪካ የሚገኙ መንግስታት ኢትዮጵያዊያን የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲዎች በሚገኙባቸው ከተሞች ሁሉ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያደርጉ እየፈቀዱ የሀገራችን መንግስት ግን ከራሱ አልፎ ሌሎችን ባዕዳን መንግስታትን እንዳንቃወም መከልከሉ አስገራሚም አሳዛኝም ነው” ሲሉ አያይዘው ገልፀዋል።
ባለፈው እሁድ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም መድረክ ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በከተማዋ በሚደረጉ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች እንዲሁም በቀጣይ የሚደረጉ ስብሰባዎች ስለሚኖሩ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ እንደማይቻል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝባዊ ስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ማስታወቁ አይዘነጋም። ባለፈው ቅዳሜ የክፍሉ ኃላፊ አቶ ማርቆስ ብዙነህ ይህንኑ የሚገልፅ ደብዳቤ ለመድረክ መላካቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው አርብ በሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አካባቢ የጠራው ሰልፍ እውቅና እንደሌለው በመንግስት በኩል ተገልጾ ለሰልፉ የወጡ ከሳዑዲ አረቢያ የመጡ ተሳታፊዎች ጭምር በፖሊስ መደብደባቸውና የፓርቲው አመራሮችና ጋዜጠኞች ጭምር ታስረው መፈታታቸው አይዘነጋም። (ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ)

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፋኖ አጣየና ሰከላ ከተሞችን ተቆጣጠረ | ጎንደር ታላቁ ጦርነት ተጀመረ | ፋኖ ደሴን ለመቆጣጠር ደርሷል | ፋኖ ባ/ዳር ላይ እጅግ አሳፋሪ ጥቃት አከናንቦናል"

በዶ/ር መረራ ጉዲና መፅሐፍ ላይ
ሊደረግ የነበረው ውይይት ተሰረዘ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

በቅርቡ ለሕትመት የበቃው “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞ እና የህይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ ለሕትመት በበቃው መፅሐፍ ባለፈው አርብ ሕዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ሊካሄድ የነበረው ውይይት ተሰዘረ።
ውይይቱ ተዘጋጅቶ የነበረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጀርመን ተቋም የሆነው የፍሬዲሪክ ኤቨርት ፋውንዴሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ዲፓርትመንት ጋር በመተባበር ነው። ተቋሙ ከዚህ በፊት የንባብ ባህልን በማበረታታት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በተለያዩ የሀገሪቱ ምሁራን በታተሙ መፅሐፎች ላይ ሕዝባዊና ምሁራዊ ውይይት ሲያካሂድ ቆይቷል። በህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ፕሮግራምም ላይ የመፅሐፉ ደራሲ ዶ/ር መረራን ጨምሮ ሌሎች ተጋባዥ ምሁራን አስተያየታቸውን የሚሰጡበት ፕሮግራም ተዘጋጅቶ በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢም የፕሮግራሙ ማስታወቂያ ተለጥፎ ሲያበቃ ለጊዜው ግልፅ ባልሆነ ምክንያት ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ተደርጎ የዕለቱ ዝግጅት ተሰርዟል።
የመፅሐፉ ደራሲ ዶ/ር መረራ ጉዳዩን በማስመልከት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ መፅሐፉ ኢህአዴግን ሳያስጨንቀው የቀረ አይመስለኝም ብለዋል። በተለይ ኢህአዴግ ኢትዮጵያን እየመራ ያለበት “ቀልድ” ሀገሪቱን የትም አያደርሳትም የሚለው የመፅሐፉ መደምደሚያ በኢህአዴግ ባለስልጣናት ላይ ቅሬታ መፍጠሩን አፍቃሪ መንግስት ከሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ታትመው ከሚወጡ ፅሁፎች እየተረዳሁ ነው ብለዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ዲፓርትመንት ኃላፊ ዶ/ር ካሳሁን ብርሃኑ ስለጉዳዩ ጥያቄ ቀርቦላቸው የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አዳራሹን እንደሚፈልገው በመግለፁ ዝግጅቱ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ መደረጉን ለሰንደቅ ጋዜጣ አረጋግጠዋል። የፕሮግራሙ ዋና አዘጋጅ የጀርመን ተቋም የሆነው ፍሬድሪክ ኤቨርት ፋውንዴሽን መሆኑን ጠቅሰዋል። የዚህን ተቋም የፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ያሬድ ፈቃደን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
“የኢትዮጵያ ፖለቲካና ምስቅልቅል ጉዞ እና የህይወቴ ትዝታዎች” የሚለው የዶ/ር መረራ መፅሐፍ በቅርቡ በሀገሪቱ ከወጡ የፖለቲካ መፅሐፎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።¾

ተጨማሪ ያንብቡ:  “እኛ ለማንነታችን ብንሞት ኩራት ነው፤ ወራሪ ያለቦታው ሲሞት ግን ውርደት ነው” ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

4 Comments

  1. Perfect! Now the real struggle begins in earnest.

    Our collective anger should foremost be against this alien regime and its all supporters. Saudi Arabia, Yemen and all the other barbarians would never dare to touch any other nationality who have the full protection of international norm enforced by their respective diplomatic missions. Every nation on earth except Ethiopia (not even Somalia) have government that have the national interest of its people as well as their national sovereignty. Ethiopia, however, has no government, only venomous vampires including the Saudi Al Amoudi sucking the life blood of every living thing on that land hoping to dismember it once they deemed it unusable.

    Bravo Medrek, we will support you.

    May God Save Ethiopia!

  2. I hope that the bad experience with the former “knijit”-party will not repeat itself with Medrek. It is only a strong Medrek which would give the Ethiopian people the hope of dismantling the tyrant woyane-regime from power through the ballot box. But one question mark remains unanswered: Which guaranty do we have that the woyanes wouldn’t once again steal the votes of the people? Could an international observer body also travel to the provinces to control the counting of votes and save us from daylight roberry of votes? Anyway, I hope that this tyrant regime would not stay in power until the next election!

  3. This calling of demonstration is at the right time at the right place.I am sure Suadi returnees will join the demonstration for denouncing what the TPLF/EPRDF regime has done on them in a foreign land.

  4. The ethno fascist Tigre people liberation front always places a stumbling block when Ethiopans rise together to protest against abuse , murder and humiliation of our citizens both inside and outside the country.

    Merrara Gudina claims he is part of the opposition and has been a talking shop without any substance for 21 years.

    Will this rhetoric about public demonstration by Medrek be another empty talk without action.

    What is the use of an opposition party if it does not come out in the open and oppose injustice to the citizens it says it represents.

    We have so many opposition groups like this in Ethiopia. there are in fact 93 ethnic based parties and others whit multi ethnic composition. Most of these , of course are created by TPlf and exist in name only, to provide a smoke screen for the fascist Tigre people liberation front for its bogus claims of multi party democracy in Ethiopia.

Comments are closed.

Share