September 4, 2019
1 min read

እኛ ከተፋቀርን – ከሰሎሞን ዳኞ

ከጎጃም ኮረንቲ
ሰሊጥ ከጎንደር
ከትግራይ ማሩን
ጨውን ከአፋር፡፡
የፍቅር ሙዚቃ ከወሎ ካሴት
ጥላቻን የሚያርቅ ትዝታ የሚከት፡፡
ከአዶላ ከአሶሳ ከወለጋ ወርቁን
ከሸዋ ወተቱን ቅቤና ስኳሩን፡፡
ሠንጋ ከሐረርጌ
ጋዙን ከሱማሌ
ገብስና ስንዴውን ከአርሲ ከባሌ፡፡
ከኢሉ አባቦራ ከከፋ ቅመሙን
ቡናውን ከጅማ
ከጋምቤላ ሩዙን፡፡
ወደ አርባ ምንጭ ዘልቀሽ
ጨንቻም ጎራ ብለሽ
ዓሣውን፣ አፕሉን ሙዙንም ጨምረሽ
አንች የአገሬ ቆንጆ ነይ በነፍሴ ድረሽ፡፡
አታስቢ ውዴ ቢኖር የተረሳ
አታስቢ ፍቅሬ ቢበዛ የሚያሳሳ
አለልን መርካቶ አለልን ፒያሳ፡፡
ከቶ ምን ይጠፋል ከውቧ አገራችን
ከቶ ምን ይታጣል ከኢትዮጵያ እናታችን
እኛ ከተፋቀርን ካለ አንድነታችን፡፡

Previous Story

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ተጨባጭ እውነታ ዋልታዎች ( ክፍል ፪ ) አንዱዓለም ተፈራ

96672
Next Story

የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔና የአቋም መግለጫ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop