February 24, 2019
2 mins read

ወቅቱ አማራ በርካታ ፈተናዎች ያሉበት በመሆኑ ፈተናዎቹን ለመሻገር ተደራጅቶ መንቀሳቀስ ተገቢ መሆኑን ብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ጽጌ ተናገሩ

94246

ወቅቱ አማራ በርካታ ፈተናዎች ያሉበት በመሆኑ ፈተናዎቹን ለመሻገር ተደራጅቶ መንቀሳቀስ ተገቢ መሆኑን ብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ጽጌ

ተናገሩ፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=ZdkEBlHGPDA&t=1s

ይህን የተናገሩት በዛሬው እለት በደሴ ከተማ የአማራ ወጣቶች ማህበር በወሎ በተለመሰረተበት ወቅት ነው፡፡ ጄኔራሉ በንግግራቸው ‹‹የሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ መልካም ነገሮችን ይዞ እንደመጣው ሁሉ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮችም አሉ፤ በመሆኑም መልካሙን ለማጎልበት እና ችግር ያለበትን ለማስተካከል የአማራ ወጣቶች ሚና የጎላ ነው›› ብለዋል፡፡ የአማራ ክልል የፀጥታ ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ጄኔራሉ በዚሁ ንግግራቸው የተደራጀ ሕዝብ ለአካባቢው ልማት፣ ሰላምና ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ስላለው በአማራው መካከል በፍፁም መከፋፈል መኖር እንደሌለበትም መክረዋል፡፡

‹‹ከአሁን በፊት በአማራ ክልል ውስጥ ወንድም ወንድሙን እየገደለ፣ እየዘረፈ እና እያሰቃየ እንዲኖር ሲደረግ ኖሯል፤ አሁን አንድ ሆነን መቆም መቻል አለብን›› ብለዋል ብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ጽጌ፡፡

የአማራ ወጣቶች ማኅበር በወሎ ሲመሠረት ከደቡብና ከሰሜን ወሎ ዞኖች ሁሉም ወረዳዎች እና ከኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡ ወጣቶቹ በአማራነት እና በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል ተብሏል፡፡

94243
Previous Story

የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ኢትዮጵያዊያን የቤት ሰራተኞችን በተመለከተ አዲስ ህግ አወጣ!

94249
Next Story

ከጎንደሩ ፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ጋር የተለያየው ዩጋንዳዊው አማካኝ ያሳር ሙጊርዋ በሰአታት ልዩነት ውስጥ የትግራዩን ሽሬ ከነማ እንደተቀላቀለ ተሰማ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop