February 24, 2019
2 mins read

የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ኢትዮጵያዊያን የቤት ሰራተኞችን በተመለከተ አዲስ ህግ አወጣ!

94243

 

አለ ማዲና ለተሰኘው በአረብኛ ቋንቋ ለሚታተመው ጋዜጣ መግለጫ የሰጡት በጂዳ ንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የስራ ቅጥር ኮሚቴ ሊቀመንበሩ ያህያ አል ማቅቡል እንደተናገሩት ወደሳኡዲ ለስራ የሚሄዱት ሴቶች እድሜ ከ23 አመት እንዳያንስ አዲስ መመሪያ ወጥቷል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=ZdkEBlHGPDA&t=1s

ከዚህም በተጨማሪ ሴቶቹ በአገራቸው ማሰልጠኛ ተቋም የሚሰጠውን ስልጠና ቢያንስ ለ30 ቀናት መከታተል እንዳለባቸው ጠቁመው የቤት ውስጥ ስራዎችን ማከናወን የሚችሉ ሊሆኑ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡

 

እነዚህ ሴቶች ከተላላፊ በሽታዎችና ከወንጀል ነፃ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ እንደኒገደዱም አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም አዲስ አበባ የሚገኘው የሳኡዲ አረቢያ ኤምባሲ እውቅና ወደሚሰጠው ሆስፒታል በመሄድ የስነልቦና ጤና ምርመራ ተደርጎላቸው ካለፉ ብቻ እንደሚቀጠሩ አል ማቅቡል ይፋ አድርገዋል፡፡ እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟሉ ሴቶች ከ900 ሪያል (240 ዶላር) ጀምሮ ሳኡዲ ውስጥ እንዲቀጠሩ ሁኔታዎች መቻቸታቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በተለይም ከመጪው ረመዳን የፆም ወር በፊት አገሪቱ በርካታ ሰራተኞችን ለመቅጠር እንደምትፈልግ ተናግረዋል፡፡-

94240
Previous Story

የአረና ትግራይ ስትራቴጂውን እና አማራጭ ፖሊሲውን ለመቀሌ ሕዝብ አስተዋወቀ

94246
Next Story

ወቅቱ አማራ በርካታ ፈተናዎች ያሉበት በመሆኑ ፈተናዎቹን ለመሻገር ተደራጅቶ መንቀሳቀስ ተገቢ መሆኑን ብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ጽጌ ተናገሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop