February 7, 2019
4 mins read

ማዕከላዊ ጎንደር ጭልጋ የጦር አውድማ መስላለች | በተከሰተው ግጭት የሰው ሕይወት ጠፋ | ንብረት ወደመ

93938

በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ አንዳንድ ቀበሌዎች በተቀሰቀሰ ግጭት የሰዉ ህይወት መጥፋቱንና ንብረት መውደሙ ተሰማ::

https://www.youtube.com/watch?v=QY21a9JgtmU&t=58s

በተለይ ጭልጋ ወረዳ በ”አማኑኤል ቀን ወጣ’  ቀበሌ አማኑኤል በተባለ ቦታ እና በሌሎችም አጎራባች ቀበሌዎች  በቅማንት ኮሚቴ ስም የታጠቁ ሀይሎች በርካታ ቤቶችን ማቃጠላቸው ተሰመቷል::   ቡድኑ በተመሳሳይ በአይምባ ሰቀልት አካባቢም በንፁሀን ላይ በፈፀመው ቃጠሎ የብዙዎች ሀብት የወደመ ሲሆን በርካታ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል::

የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር እንየዉ ዘዉዴ በግጭቱ የጠፋዉን የሰዉ ህይወትና ንብረት ልክ ግን  ለመናገር ባይደርፍሩም ግጭቱ አሁንም ድረስ አለመብረዱን ኮማንደሩ አረጋግጠዋል::

በዚህ አካባቢ በተነሳው ከፍተኛ ግጭት የመተማ ከተማን ከጎንደርና ከባህርዳር የሚያገናኘዉ መንገድ በመዘጋቱ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ሳይቀሩ መቆማቸውን የአካባቢው ኔዋሪዎች ይናገራሉ::

በሌላ በኩል ቤደምቢያ ወረዳ ከፍተኛ በቅማንትና አማራ በሚል በተከፋፈሉ ወገኖች ግጭት መኖሩ ታውቋል:: በዚህም ግጭት በሰው ሕይዎትና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ምንጮች የገለጹ ሲሆን  የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

 የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አሰማኸኝ አስረስ በደምቢያ ወረዳ እየተስተዋለ ባለው  አለመረጋጋት በሰው ሕይዎትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል ይህንንም  የአማራ ክልል መንግሥት ያወግዛል ብለዋል::  “ግጭቱ ሁለቱንም ሕዝቦች የማይወክል መሆኑ በተጨባጭ ማሥረጃ ተረጋግጧል:: ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው በሚል የተያዙ ተጠርጣሪዎች አሉ;; የእሥር ማዘዣ የወጣባቸውአሉም”  ያሉት አቶ አሰማኸኝ  ግጭቱ ዳግም ያገረሸበት ምክንያት አካባቢውን ለማረጋጋት ተሰማርቶ የነበረው 24ኛ ክፍለ ጦር ወጥቶ 33ኛ ክፍለ ጦር ለግዳጅ ሊገባ እያለ ጥር 24/2011 ዓ.ም መንግሥት ‹‹የተደራጁ ቡድኖች›› ያላቸው አካላት በጸጥታ አካላት ላይ ጥቃት በማድረሳቸው ነው፡፡

ራሱን የቅማንት ኮሚቴ ነኝ ዕያለ የሚጠራው ቡድን አብዛኞቹ ቅማንቶች አለመሆናቸውና በ እነርሱ ስም የሚዋጋው ሕወሓት መሆኑ በተደጋጋሚ ሲነገር ቆይቷል:: ሕወሓት ጎንደርን ለ27 ዓመታት በኢኮኖሚው አድቅቋታል አሁን ደግሞ በጦርነትና እርስ በ እርስ ግጭት ሊያጠፋት ቆርጦ ተነስቷል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች በርካታ ናቸው::

1 Comment

  1. የሃገሬ ሰው የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል ይላል። አሁን እንሆ በአማራና በቅማንት መካከል ምን ልዮነት ኑሮ ነው ሰው ሰውን የሚገድለው? ይዘገንናል። እረፍት ያጣች ምድር። የጭቃና የኖራ ቤት አቃጠልክና ጅግና ነኝ ብለህ ትፎክራለህ። ሰው ወንድሙንና እህቱን ገድሎ በደስታ የሚሽልልባት ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። በመሰረቱ ለዛሬው ትንኮሳና የጎሳና ጎጥ የወረርሽኝ በሽታ ተጠያቂው ወያኔና ሻቢያ ናቸው። ባሩድ አሽተው በረሃ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ስራቸው ሁሉ የድርቡሽ ነው። ዛሬም ቢሆን በእርጅና ተንኮል መስራታቸው እንዳለ ነው። እሳት ሰጥተው አይዞህ እያሉ ሌላው ሌላውን እንዲያጠቃ የሆነው እነርሱ በቀደዱት የተጣመመ የፓለቲካ ፈርና ቋስቋሽነት ነው።
    በቋንቋ፤ በሃይማኖት፤ በዘርና በሌላው (ክልላዊ በሽታ) ተይዘን ሃተፍ ተፍ ስንል ጀንበር ትጠልቃለች። ይህን የእኛን ደካማ ጎን ከቅርብና ከሩቅ ያዮ ጠላቶቻችንም ነዳጅ እያቀበሉ አይዞህ በማለት አንድ ሌላውን እንዲያጠቃው ዝንተ ዓለም ይጥራሉ። የሃበሻው ምድር ግን ገና አልነቃም። ጠላቱንና ወዳጁን ለይቶ አላወቀም። ሰርቶ ከመኖር ይልቅ ገድሎ መዝረፍና ለከፋፋዮችና ለሃገር አጥፊዎች መሳሪያ መሆንን ይመርጣል። አሁን በጎንደርና በዙሪያው የምንሰማውና የምናየው ይህኑ ነው። ወያኔ በመሰረቱ እሳትን እንደ ፓለቲካ መሳሪያ መጠቀም የጀመረው ገና በረሃ እያለ ነው። ሰዎችን ለመግደል ከሚጠቀምበት አንድ ዘይቤው በጭስና በእሳት ማስወገድ ነው። ይህ ከሚያልፍ ወንዝ የተቀዳ ታሪክ አይደለም። በላይና ታች አርማጭሆ፤ በወልቃይትና ጠገዴ እልፍ የሃገራችን ሰዎችን ያጠፋበት መንገድ እንደነበር ዛሬም የዓይን ምስክሮች ይነግሩናል። ሞት ያስወገዳቸው ጠ/ሚ መለስ ለአንድ የአሜሪካ ልዑካን “አማራን አንወድም፤ እነርሱ ወደ ስልጣን ከመጡ ሰላም አይሆንም” በማለት ለመናገራቸው ወያኔ የቱን ያህል የተጣረሰ ፓለቲካ እንዳለው ያመላክታል። መሆን የነበረበት ከየትኛውም የሃገሪቱ የመጣ ይሁን መመዘን ያለበት በአስተዳደር ብቃቱ እንጂ በዘርና በቋንቋው ወይም በሃይማኖቱ መሆን የለበትም። የወያኔው አፈቀላጤ አቶ ጌታቸው ረዳ ” አማራና ኦሮሞ አንድ ሆኑ ማለት እኛ የቤት ስራችንን አልሰራንም ማለት ነው” በማለት በጋዜጠኞች ፊት ያለፍረት ሲደነፉ ማብራሪያ የጠየቀ የለም። ነገሩ ቀላል ነው። አኖሌን ያቆምነው አንድ እንድትሆኑ ሳይሆን እንድትከፋፈሉ ነው ማለቱ ነበር። አሁን በጎንደርና በዙሪያዋ እሳቱ፤ ግድያው፤ አፈናው፤ ቅሚያው ሁሉ በወያኔ የተቀነባበረ እንደሆነ ያለፈ ተግባራቸው መረጃ ነው። የአማራ ተወካይ ተብየወች ባህር ዳር ላይ ተቀምጦ በስማ በለው በደረሰ ወሬ ሁሌ የተጣመመ መግለጫ ከመስጠት ይልቅ ዝርዝር መረጃ ያለውና የሞቱት ሰዎች ስም፤ የጠፋው ሃብት፤ ዝርፊያና ግድያው የተፈጸመበት ጊዜና ስፍራ ከአውራጃ/ወረዳ/ም/ወረዳ/ቀበሌ በጽሁፍ በመቀበል ይፋ ማድረግ ያስፈልጋል። የተፈጠረውም በደል በቪዲዮና በስፍራው ባሉ ሰዎች ቃለ መጠየቅ ጋር ተጠቃሎ ለህዝብ ጀሮ መድረስ አለበት። ያለበለዛ ባህር ማዶ ላይ ቆሞ ሞረሽ ቢሉ ሰሚ የለም።

Comments are closed.

93934
Previous Story

የዕለቱ የዘ-ሐበሻ ዜናዎችን ይመልከቱ – በርካታ መረጃዎች

93941
Next Story

የሶማሌ ክልል ያለመከሰስ መብታቸውን ያነሳባቸው አብዛኞቹ ባለስልጣናት ከሃገር አምልጠዋል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop