January 16, 2019
2 mins read

የቀድሞ ጠ/ሚ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ

የቀድሞ ጠ/ሚ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=epx_GOJUaUQ
የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ለሃገሪቱ የቱሪዝም እድገት የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት ጠይቋል፡፡ የቱሪዝም ዘርፍ ለማሳደግ ከኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ትናንት በተካሄደው ውይይት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ወ/ት ሌንሴ መኮንን እንደገለጹት፣ ቱሪዝም ያለ ኪነጥበብ ባለሙያዎች እድገቱን ማፋጠን አዳጋች ነው፡፡ ከቱሪዝም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ኪነ ጥበብ ሀገራዊ ወግ ባህልና እሴቶችን በማስተዋወቅና ከፍተኛ ሚና አለው፡፡

የድርጅት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰርፀ ፍሬስብሃት በበኩላቸው፣ ኪነ ጥበብ የቱሪዝም ዘርፍ በማሳደግ የላቀ ሚና እንዳለው ጠቁመው፣ ለዚህም ተቋማቸው በአዲስ መልክ የተጠናከረ ስራ ለመስራት እቅድ መያዙን አንስተዋል፡፡ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችም በጥበብ ስራቸው ውስጥ የሀገሪቱን መለያ/ብራንድ /እና ልዩ ልዩ እሴቶችን በማስተዋወቅ ለቱሪዝም ዘርፉ የላቀ ሚና ማበርከት እንደሚችሉ አመልክተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞ ጠ/ሚ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መሾማቸውን ለመረዳት ችለናል፡፡

93745
Previous Story

በምዕራብ ኢትዮጵያ ህገ ወጥ ትጥቅ ታጥቀው የህዝቡን ሰላም ሲያውኩ የነበሩ 835 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የምእራብ ኢትዮጵያ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ

93751
Next Story

የሲሲዲ መኖሪያ መንደር መስራች ፍርድ ቤት እንዲቀርበ ታዘዘ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop