በአሜሪካ ታዋቂው ኢትዮጵያዊ አቶ ሰለሞን በቀለ አረፉ

(አድማስ ራድዮ) በአሜሪካን አገር ቀድመው ከመጡ ኢትዮጵያውያን አንዱ የሆኑትና፣ በበርካታ የማህበራዊና የፖሊቲካ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ የነበሩት አቶ ሰለሞን በቀለ ማረፋቸው ተሰማ። ቀድሞ አትላንታ፣ ከዚያም በሜሪላንድ የኖሩት አቶ ሰለሞን በቀለ የራሳቸው የታክሲ ኩባንያ በመመስረት ከቀዳሚ ኢትዮጵያውያን አንዱ ነበሩ።
https://www.youtube.com/watch?v=ncwpPfdrV3E&t=991s
የየሎ ካብ ታክሲ ኩባንያ ባለቤት የነበሩትና በኋላም በሽያጭ ያዛውሩት አቶ ሰለሞን፣ በሜሪላንድ የደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ቤተክርስርቲያን ህንጻ ሲገነባም ትልቅ አስተዋጾ ማድረጋቸውም ይታወሳል።

በርካታ ታክሲዎችና የኡበር ተሽከርካሪዎችን በደምበኝነት ያቀፈ የኢንሹራንስ ድርጅትም ነበራቸው።

የጸሎት ፕሮግራም በመጪው ጃንዋሪ 12 ቅዳሜ ጠዋት 9 ሰዓት ላይ በዚያው በሜሪላንድ ደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን የሚካሄድ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ቀን 1 ፒ ኤም ላይ በፌር ፋክስ ሚሞሪያል መቀበሪያ ቦታ ቀብራቸው እንደሚፈጸም አድማስ ራድዮ ከአትላንታ ዘግቧል::
አቶ ሰለሞን በቀለ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይ ተባበሩ አልያም ተሰባበሩ በሚል በዋሽንግተን ዲሲ ትልቅ ስብሰባ በማዘጋጀት ቅንጅት እንዲፈጠር ምክንያት ከሆኑት ወገኖች መካከል ስማቸው ይጠቀሳል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጁኔይዲ ሳዶን ወደ ኬኒያ መሰደድ ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ ምላሽ ሰጠ

1 Comment

  1. አቶ ሰለሞንን ለመጀመርያ ጊዜ የተዋወቅኩት ወደ ቨርጅንያ ተዛውሬ መኖር በጀመርኩበት ጊዜ ነበር:: ስሜን ስነግረው የሱ ምላሽ ቤተሰብህን አውቃለሁ ወንድምህም በጣም ወዳጄ ነው ነበር:: እኔም እሱን ለብዙዘመን የማውቀው ያህል ነበር የተሰማኝ:: በሚቀጥሉት ዓመታት ከአቶ ሰለሞን ጋር ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አብሮ የመስራት እድል አጋጥሞኝ ነበር:: ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ማዕከል የቦርድ አባልና ሊቀመንበር በነበርኩበት ዘመን ማዕከሉ የሱ እርዳታና ማበረታታት ተለይቶት አያውቅም:: ለምሳሌ ያህል በመኖርያ ቤቱ ለማዕከሉ የገንዘብ ማሰበሰብ ዝግጅት አድርጎ እርዳታውን አበርክቶአል:: ማዕከሉም የራሱ ቤት ባለቤት ለመሆን በሚጥርበት ዘመን የአቶ ሰለሞን እርዳታ ፊት ቀደም ነበር::

    እምነትን በተመለከት አቶ ሰለሞን የደብረ ገነት መድህኃኔዓልም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንጋፋ አባል ነበር:: ቤተክርስቲያኑን በልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ከማገልገል በላይ በየጊዜው እርድታውን ከመለገስ ወደሁዋላ ብሎ የማያውቅ
    ምእመን ነበር:: ይህን በቅርብ ያየሁት ቤተክርስቲያናችንን በቦርድ ሊቀመንበርነት ባገለገልኩበት ዘመን ነው:: ምን ላግዝህ ብቻ ሳይሆን ሲጠየቅም ቀድሞ ደራሽ ነበር::

    ወንድማችንን በማጣታችን በጥም እናዝናለን:: እግዚአብሔር ቤተሰቦቹን ያጽናና የሱንም ንፍስ በገነት ያሳርፍ::

    ዳዊት ተክሉ

Comments are closed.

Share