December 14, 2018
2 mins read

33 የአዲስ አበባ ወጣቶች በ15 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤት የሰጠው ትእዛዝ ታገደ

የኦነግን አቀባበል ተከትሎ በአዲስ አበባ ቡራዩና አካባቢው ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘና በሽብርተኝነት የተከሰሱት የአዲስ አበባ ወጣቶች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ከቀናት በፊት 17 ያህል በተመሳሳይ ክስ የቀረቡ የከተማው ወጣቶችን ክስ ፍርድ ቤቱ ወደግድያ ወንጀል እንደቀየረው መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት 33 ተጠርጣሪዎች የቀረቡ ሲሆን መርማሪ ፖሊስም ያቀረበው ክስ ሽብርተኝነት ነበር፡፡ በዚህ መሰረት መርማሪ ፖሊስ በወቅቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች የሙሉ ምስክርነት ቃል ለመቀበል እንዲሁም ተጎጅዎችን በአካል ማነጋገር አስፈላጊ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት 28 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው እያቀረባቸው ያለው ሀሳቦች ተደጋጋሚና የተከሳሾችን የዋስትና መብት የሚጋፋ በመሆኑ በነፃ እንዲያሰናብታቸው ወይም ደግሞ የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

የግራ ቀኙን ክርክር የተመለከተው ፍርድ ቤቱ የፖሊስን ጥያቅ ውድቅ በማድረግ ተከሳሾ በ15 ሺ ብር ዋስ እንዲፈቱ ትእዛዝ አስተላልፎ የነበረ ቢሆንም መርማሪውና አቃቤ ህግ ይግባኝ በመጠየቃቸው የዋስትናው ትእዛዝ ታግዷል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=YJYMYnduprQ&t=125s

93123
Previous Story

ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባ ሊደረጉ የነበሩት ህዝባዊ ሰልፎች ተራዘሙ

mekelle city
Next Story

በመቀሌ የዳቦና የስንዴ እጥረት ተከስቷል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop