November 22, 2018
2 mins read

የእነአብዲ ኢሌ የዛሬ የፍርድ ቤት ቀረቡ | ፖሊስ 50 አስከሬን አውጥቶ እንዳስመረመረ ገለጸ

92660

የቀድሞው የኢትዮ ሱማሊ ክልል ፕሬዚደንት አብዲ ኢሌ ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ጉዳያቸውም ለህዳር 27 ቀን 2011 ዓ.ም. ተቀጥሯል፡፡ በዛሬው ችሎት ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ እስካሁን የደረሰበትን የምርመራ ውጤት አስረድቷል፡:

፡ በዚህም መሰረት በተጠርጣሪዎቹ አማካኝነት በጅግጅጋና አካባቢው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በደረሰው ጉዳት 300 ሚሊየን ብር የሚገመት የንብረት ውድመት እንዳጋጠመ ተናግሯል፡፡

እንዲሁም ከሃምሌ 26 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. በዘርና በሃይማኖት እየተለዩ ሰዎች መገደላቸውንና በጅምላ መቀበራቸውን አስረድቶ ይህን በተመለከተም በፎቶግራፍ የተደገፈ ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ አሳይቷል፡፡ በአጠቃላይ ከ2004 ጀምሮ የክልሉን አስተዳደር በተቃወሙ 200 ግለሰቦች ላይ ግድያ እንደተፈፀመ የገለፀው ፖሊስ ለዚህም ተጠርጣሪዎቹን ተጠያቂ አድርጓል፡፡ ከ2004-2010ዓም ድረስ በሶማሌ ክልል የፍትህ ጥያቄ ያነሱ 200 ሰዎች ፀረ ሰላም ሀይሎች እየተባሉ በግፍ በአደባባይ በጠራራ ፀሀይ እየተረሸኑ በጅምላ ተቀብረዋል። እስካሁን 50 አስክሬን አስወጥተን እያስመረመርን ነው ሲልም ፖሊስ ለችሎቱ አስረድቷል::

ከአብዲ ኢሌ ጋር ሶስት ግለሰቦች በክሱ ላይ የተካተቱ ሲሆን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ደንበኞቻቸው እንዲለቀቁ ቢጠይቁም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበላቸው ቀርቷል፡፡ ፖሊስ ተጨማሪ የተገደሉ ሰዎችን ቤተሰቦች እስካፈላልግ ጊዜ ይሰጠኝ በማለቱ መዝገቡ ለህዳር 27 ተቀጥሯል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=W20KYng_SXM

92656
Previous Story

የጌታቸው አሰፋ የቀኝ እጅ ዶ/ር ሐሺም ቶፊቅ ታሰረ

92664
Next Story

በዛሬው እለት የተሾሙት ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የመጀመሪያ ስራ ይፋ ሆነ፡፡

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop