November 19, 2018
4 mins read

የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ አዲስ ክስ ተጨመረ | ፖሊስ የሜ/ጀ ክንፈ ወንድም አቶ ኢሳያስ ዳኘው በባንክ ያላቸውን ገንዘብና ንብረታቸውን ማስረጃ አቅርቦ ዋስትና ራሳቸው ያቁሙ ሲል ጠየቀ

92600

የቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት የስራ ባልደረባ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ዛሬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት ዛሬ ቀረቡ:: ፖሊስም ከሰኔ 16ቱ የቦምብ ፍንዳታ በተጨማሪነት አዲስ ክስ ይዞ በመምጣት በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።

አቶ ተስፋዬ የደህንነት መምሪያ ሀላፊ ሆነው ሲሰሩ ሰዎችን በሽብር ተጠርጥራችኋል በሚል በስውር እስር ቤት በማሰርና በማሰቃየት፥ እርቃናቸውን በካቴና አስረው ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ በማቆየት፣ ግለሰቦችን ባልተገባ መልኩ ለሽብር መልምለው ወደ ኤርትራ በመላክ እንደጠረጠራቸው ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቶ ከዚህ ባለፈም በሽብር ከተጠረጠሩ ሰዎች ላይ ገንዘብ በመቀበል እና በሀዋላ ከተጠርጣሪዎች ላይ ህገ ወጥ ገንዘብ በመቀበል በሰብዓዊ መብት ጥሰትና በሙስና ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁም ያለው ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅም 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀን ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

አቶ ተስፋዬ በሰጡት ምላሽ እርሳቸው የተጠረጠሩበት ጉዳይ በግልጽና በተናጠል እንዳልቀረበ በመግለጽ፥ እርሳቸውን ለመያዝ በቂና ዝርዝር ጉዳይ አለመኖሩን አስረድተዋል። በተጨማሪም ሀብት የመፍጠር ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ሃብት ማፍራታቸውንና ለአራት ወራት ፍርድ ቤት እየተመላለሱ መሆኑን በመጥቀስ፥ ሃብት ከማፍራት ጋር ተያይዞ ሀምሌ 5 ቀን 2010 ዓ.ም ቤታቸው መበርበሩንና ምርመራው በወቅቱ ማለቅ ነበረበት ብለዋል። አሁን ላይ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜም ሊሰጥ አይገባም በማለት ተቃውመው ነበር። ችሎቱ ግን አቶ ተስፋዬ በተጨማሪነት የተጠረጠሩበት ወንጀል በተብራራ መልኩ እንዲቀርብ አዞ ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን በመፍቀድ ለህዳር 24 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ይህ በ እንዲህ እንዳለ ባለፈው ሳምንት በሌብነት ተጠርጥረው የታሰሩት የሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው ወንድም አቶ ኢሳያስ ዳኘው “ገቢዬ አነስተኛ ነው; ጠበቃ መንግስት ያቁምልኝ” ያሉት ሀሰት መሆኑን ዛሬ ፖሊስ በማስረጃ ለችሎት አቅርቧል።
– G+1(2million የሚያወጣ) 6 ክፍል ያለው ቪላ
– ባለ 3 ክፍል የጋራ መኖሪያ
– ቶዮታ ኮሮላ ሎደር፣
– አምበሳ ባንክ አክሲዮን በተጨማሪም በዳሽን እና አዋሽ ባንክ ገንዘብ ስላለቸው በግላቸው ጠበቃ ያቁሙ ። ፍርድ ቤቱን በማሳሳታቸው አስተማሪ ቅጣት ይሰጥ ሲልም ፖሊስ ችሎቱን መጠየቁ ተሰምቷል::

“25 የአንበሳ ባንክ አክሲዮን፣ በንግድ ባንክ 40ሺ ብር፣ አምበሳ ባንክ 8000 ብር ዳሽን 11ሺ ብር ወዘተ በማለት ዳኛው በዝርዝር በፖሊስ የቀረበውን ማስረጃውን ካነበቡ በኋላ ችሎቱ በቂ ሀብት ያላቸው መሆኑን ስላረጋገጠ በመንግስት የተመደቡትን ጠበቆች አንስቷል በማለት ወስነዋል:: በዚህም መሰረት አቶ ኢሳያስ የራሳቸውን ጠበቃ አቁመው ይከራከራሉ ማለት ነው::
https://www.youtube.com/watch?v=pXfWMmUXIks

92597
Previous Story

በድሬዳዋ በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አለፈ፣ ቤቶች ተቃጠሉ

Next Story

ዶ/ር አብይ አህመድ  በአዲስ አበባ የለገሀር የተቀናጀ መንደር ግንባታ ፕሮጅክትን መርቀው በከፈቱበት ወቅት ያደረጉት ንግግር

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop