November 19, 2018
1 min read

ጀነራሎች እና ስመጥር ባለሃብቶች እየተዝናኑ የሚደራደሩበት ጎልፍ ክለብ ጭር ማለቱ ተሰማ

92584

በመከላከታ ሠራዊት ፋውንዴሽን ሥር የተቋቋመውና ጀነራሎች እና ነጋዴዎች የሙስና ድርድር ያደረጉበታል የሚባለው ጎልፍ ክለብ መዝናኛ ከወትሮው በተለየ ጭር ብሎ መሰንበቱ ተገለጸ:: ትናንት በአዲስ አበባ ታትሞ በወጣው ፍትህ ጋዜጣ ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እንደገለጸው በተለይ ሮብ አርብ ቅዳሜ ክራማው የሚደምቀው ይህ ክለብ የለጋስ ከበርቴዎች እና የጀነራሎች በተለይም ጀነራል ሳሞራ የኑስ; ሜጀነራል ብርሃነ ነጋሽ; ሜጀር ጀነራል መሃሪ ዘውዴ መዝናኛ እንደሆነ ተናግሯል::

“የጀነራል መኮንኖች መዝናኛ ጎልፍ ክለብ የተጋነነ ካፒታል ባይኖረውም ከባባድ የንግድ ስምምነቶች ሲካሄዱበት መቆየቱ ይነገርለታል:: ስመ ጥር ባለሃበቶች ከውጭ ሃገር የሚያስገቧቸውን እቃዎች በፋውንዴሽኑ በኩል ያለቀረጥ ለማሳለፍ ይደራደሩበታል:: ጀነራሎቹ ለድርጅታቸውም ሆነ ለግል ጉዳያቸው የሚሸምቱትን በክለቡ ስብ ሳያስቀርጡ ለማስገባታቸው ጥቆማዎች አሉ” ያለው ተመስገን በአሁኑ ወቅት የግቢው መንፈስ ተቀይሯል ይላል::

Watch
https://www.youtube.com/watch?v=-q8i19IEiLA&t=491s

92581
Previous Story

በሃገሪቱ ሰሞኑን እየተወሰደ ባለው እርምጃ የተነሳ የጸጥታ ጥበቃው መጠናከሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ገለጹ

92587
Next Story

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ግርማ ዋቄ ሃላፊነታቸውን የለቀቁት በሕወሓት ሰዎች “ያልንህን ካልሠራህ” ስለተባሉ መሆኑን ገለጹ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop