በመከላከታ ሠራዊት ፋውንዴሽን ሥር የተቋቋመውና ጀነራሎች እና ነጋዴዎች የሙስና ድርድር ያደረጉበታል የሚባለው ጎልፍ ክለብ መዝናኛ ከወትሮው በተለየ ጭር ብሎ መሰንበቱ ተገለጸ:: ትናንት በአዲስ አበባ ታትሞ በወጣው ፍትህ ጋዜጣ ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እንደገለጸው በተለይ ሮብ አርብ ቅዳሜ ክራማው የሚደምቀው ይህ ክለብ የለጋስ ከበርቴዎች እና የጀነራሎች በተለይም ጀነራል ሳሞራ የኑስ; ሜጀነራል ብርሃነ ነጋሽ; ሜጀር ጀነራል መሃሪ ዘውዴ መዝናኛ እንደሆነ ተናግሯል::
“የጀነራል መኮንኖች መዝናኛ ጎልፍ ክለብ የተጋነነ ካፒታል ባይኖረውም ከባባድ የንግድ ስምምነቶች ሲካሄዱበት መቆየቱ ይነገርለታል:: ስመ ጥር ባለሃበቶች ከውጭ ሃገር የሚያስገቧቸውን እቃዎች በፋውንዴሽኑ በኩል ያለቀረጥ ለማሳለፍ ይደራደሩበታል:: ጀነራሎቹ ለድርጅታቸውም ሆነ ለግል ጉዳያቸው የሚሸምቱትን በክለቡ ስብ ሳያስቀርጡ ለማስገባታቸው ጥቆማዎች አሉ” ያለው ተመስገን በአሁኑ ወቅት የግቢው መንፈስ ተቀይሯል ይላል::
Watch
https://www.youtube.com/watch?v=-q8i19IEiLA&t=491s