November 16, 2018
3 mins read

ግብፅ የህዳሴው ግድብ ድርድሩ እንዲፋጠን ጠየቀች

92553

ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሚደረገው ውይይት እንዲፋጠን እንደምትፈልግ ማስታወቋን አልሻረቅ አል አውሳት የተሰኘው የአገሪቱ ጋዜጣ ዘገበ፡፡ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ ለአፍሪካ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ አዲስ አበባ በተገኙበት ወቅት ይህን ማስታወቃቸውን ጋዜጣው አስረድቷል፡፡

ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያው አቻቸው አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ጋር በአዲስ አበባ ተገናኝተው በግል ባደረጉት ውይይት የግብፅን አቋም እንደዳስረዱ የዘገበው ጋዜጣው ወደፊት ግድቡን በተመለከተ የሚደረገው ድርድር እንደከዚህ ቀደሙ የተንጓተተ ከመሆን ይልቅ እንዲፈጥን መጠየቃቸውን ገልጿል፡፡ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ረቡእ እለት ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባ በተደረገው ውይይት ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች መታየታቸውን አስታውቋል፡፡ በግድቡ ውሃ አሞላል ዙሪያ የተነሳውን ውዝግብ ለመፍታት በግብፅ፣ በሱዳንና በኢትዮጵያ መሀከል ባለፈው ሚያዚያ ወር የሶስትዮሽ ድርድር መደረጉ ይታወሳል፡፡

ከድርድሩ በኋላ መከናወን ባለባቸው የድርድሩ አፈፃፀሞች ላይ መንጓተት እንደታየ በመመልከት ግብፅ ቅሬታ እንደተሰማት መናገሯ ነው የተዘገበው፡፡ የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አህመድ ሀፌዝ ለአልሻረቅ አል አውሳት ጋዜጣ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ጉዳዩን በጥቂት ቀናት ውስጥ እልባት እንደምትሰጠው ቃል ገብታለች፡፡ ሀፌዝ ሲናገሩም ‹‹የኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሶስቱ አገራት መሀከል ያለው ድርድር እንዲቀጥል የሚያስፍል መፍትሄ በጥቂት ቀናት ውስጥ ይዛ ትመጣለች›› ማለታቸውን ጋዜጣው አስረድቷል፡፡

የግብፁ ፕሬዚደንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ባለፈው ወር በግድቡ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖረው ግንኙነት ለፖለቲካ ፍጆታ እንደማይውል ቃል መግባታቸውንም ጋዜጣው አውስቷል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=x9Np1L1BJWY

92537
Previous Story

ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው የሰው እጅ እንዳላይ መንግስት ጠበቃ ያቁምልኝ አሉ | ወንድማቸውና የቀድሞዋ የETV ጋዜጠኛ ታሰሩ

92556
Next Story

የቀድሞው የብሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ምክትል ኃላፊ ጠበቃ አቁመው እንዲከራከሩ ጊዜ ተሰጠ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop